እንደተፈራው ዶክተር ሀይለየሱስ ባዘዘው ከአካል ብቃት ምዘናው ታግደዋል።
ከ25ቱ ዋና ዳኞች አንዱ የነበረው ዶክተር ሀይለየሱስ ባዘዘው ከዳኞች ኮሚቴ ዲፓርትመንት ሃላፊው መፈተን እንደማይችል በመገለፁ ከምዘናው ውጪ ተደርጓል። በዳኞች ኮሚቴው የቀረበው ክስ በዲሲፕሊን ኮሚቴ ውድቅ መደረጉ ያልተዋጠለት የዳኞች ኮሚቴ የፍትህ አካላቱ የወሰኑትን ውሳኔ በአምባገነንነት አለመቀበሉ ከጀርባው የተማመነበት ሃይል ይኖር ይሆን የሚል ጥያቄንም አስነስቷል።
ከዲሲፕሊን ኮሚቴ ውሳኔው መልስ አርቢትሩ በደብዳቤ ላቀረበው ጥያቄ ምላሽ የነፈገው ዳኞች ኮሚቴ ዶክተሩ ለፈተናው ወጪ አውጥቶ ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ቢመጣም ልምምዱን ከሰራ (ለመፈተን ሰውነቱን ከሁሉም ዳኞች ጋር ካሟሟቀ) በኋላ ሊፈተን ሲል የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ጸሃፊነትን ደርቦ የያዘው የዲፓርትመንቱ ሃላፊ አትችልም ብሎ እንደመለሰው የደረሰን መረጃ ያስረዳል።
የዳኞች ኮሚቴ ተግባር አሁንም እያነጋገረ ሲሆን ዳኞችን ማረም መመለስ ማስተካከል ሳይሆን እልህ እየተጋባ እርምጃ መውሰድ መቀጠሉ ተገቢነት እንደሌለው በመግለጽ ጽ/ቤቱ ፣ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ወይም ፕሬዝዳንቱ ጣልቃ በመግባት አደብ ሊያስገዙ እንደሚገባ የስፖረት ቤተሰቡ ጥሪ ሆኗል።
- ማሰታውቂያ -
አርቢትሩ ምዘናውን ለመካፈል ከባህርዳር አዲስ አበባ ቢመጣም እንዳይፈተን መደረጉ ታውቋል። ይግባኝ የጠየቀው የዳኛ ኮሚቴ ዶክተሩን ያገደበት የህግ መብት እንደሌለው ቢታወቅም እንደተጠበቀው ይግባኝ ጠይቀናል በሚል ሰበብ በስልጣናቸው ከአካል ብቃት ምዘናው ውጪ ማድረጋቸው አነጋጋሪ ሆኗል።


