አርባምንጭ በስራ አስኪያጁ ፍቃድ ከቦታው ሲነሱ መቻል የቀድሞውን ቡድን መሪ ስራ አስኪያጅ አደረገ።
በሊጉ ግርጌ ስር ተቀምጦ የሚገኘው አርባምንጭ ከተማ ለሁለተኛ ጊዜ ካለፈው አመት አጋማሽ ጀምሮ አርባምንጭ ከተማን በስራ አስኪያጅነት የመምራት ዕድልን ያገኙት አቶ ዳዊት ሀይለማርያም ከስራ አስኪያጅ ቦታ ላይ ከአንድ አመት በኋላ በገዛ ፍቃዳቸው መነሳታቸውን ያገኙት መረጃ አመላክቷል።
ከስራ አስኪያጁ ጋር ከሳምንታት በፊት በነበረኝ የስልክ ቆይታ ስራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩ አንዳንድ ሰዎች ጣልቃ ይገቡባቸው እንደነበር ነግረውኝ ነበር። በሌላ ዜና ደግሞ መቻልን ዘለግ ላሉ አመታት ቡድን መሪ በመሆን ያገለገሉት እና በያዝነው አመት ከቦታው ተነስተው የነበሩት ኮሮኔል አለሙ ዘነበ በስራ አስኪያጅ ቦታው ላይ ከቀናት በፊት ተሹመዋል።


