በሲዳማ ቡና ውስጥ ዘለግ ላሉ አመታት ቆይታን ያደረገው አጥቂ ወደ አዲስ አዳጊው ክለብ አምርቷል።
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ የመጀመሪያ የተሳትፎ ዘመኑን ዘንድሮ የሚያደርገው የአሰልጣኝ ቱሉ ደስታው ነገሌ አርሲ በባቱ ከተማ አዳዲስ ተጫዋቾችን ከነባሮቹ ጋር በመያዝ ሲያደርግ ከነበረው ዝግጅት በኋላ በቀጣዩ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር የመክፈቻ ጨዋታ ከአርባምንጭ ከተማ ጋር በአዲስ አበባ ስታዲየም መርሀግብሩን የሚያደርግ ሲሆን ቡድኑን ለማጠናከርም ክለቡ አጥቂው ይገዙ ቦጋለን ወደ ስብስቡ ለማካተት መቃረቡን ሀትሪክ ስፖርት ያገኘችው መረጃ ይጠቁማል።
ከሲዳማ ቡና ወጣት ቡድን መነሻውን ካደረገ በኋላ በዋናው ቡድን ውስጥ የስድስት አመታት ቆይታን ያደረገው የ2016 የሊጉ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ቀጣዩ ቡድኑ አዲስ አዳጊው ነገሌ አርሲ መሆኑ ተሰምቷል።



