*… የሶስቱ አሰልጣኞች ሲቪ ተገምግሟል…
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የፋሲል ከነማው አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌን የዋሊያዎቹ ዋና አሰልጣኝ እንዲሆን መስማማቱ ይታወሳል።
አሰልጣኙ በፌዴሬሽኑ አመራር ይሁንታ ያገኘው የሱን የአሰልጣኝ ውበቱ አባተና የአሰልጣኝ በጸሎት ልዑልከገድ ሲቪን ከመረመረ በኋላ ብልጫ አለው በሚል እንደሆነ ታውቋል።
በነገራችን ላይ ሶስቱም አሰልጣኞች ይህን አያውቁም ሲቪም አላስገቡም.. ስራ አስፈጻሚው ጉዳዩ በሚመለከተው አካል የቀረበለትን ሲቪ መርምሮ አሰልጣኝ ዮሀንስን እንደመረጠ ከታማኝ ምንጭ መረጃውን አግኝቻለሁ….።
- ማሰታውቂያ -

ለዋሊያዎቹና ለአሰልጣኙ መልካም የሰራ ጊዜ እንዲሆን እመኛለሁ


