By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: አዳማ ከተማ እና ፋሲል ከነማ ለተከታታይ 5ኛ ጨዋታ አቻ ሲለያዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ሳይሸናነፉ ተለያይተዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ኢትዮ-ኤሌክትሪክአዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባፋሲል ከነማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወልዋሎዜናዎች

አዳማ ከተማ እና ፋሲል ከነማ ለተከታታይ 5ኛ ጨዋታ አቻ ሲለያዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ሳይሸናነፉ ተለያይተዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 2 months ago
Share
SHARE

አዲስ አበባ ላይ የተደረጉት ጨዋታዎች ግብ ሳይቆጠርባቸው ተጠናቀዋል

በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ13ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ አዲስ አበባ ላይ የተደረጉት ጨዋታዎች ያለ ግብ ተጠናቀዋል።

በቀዳሚነት ከቀን 07:00 ጀምሮ የተደረገው የአዳማ ከተማ እና የፋሲል ከነማ ጨዋታ የመጀመሪያ አጋማሽ የአዳማ ከተማ የበላይነት የታየበት ነበር።

በአጋማሹ ከተጋጣሚያቸው በተሻለ የግብ ዕድሎችን መፍጠር የቻሉት አዳማ ከተማዎች ኳስ እና መረብ ማገናኘት የሚችሉባቸውን አጋጣሚዎች መጠቀም ሳይችሉ ቀርተዋል።

- ማሰታውቂያ -

የመጀመሪያ ሙከራቸውን በ4ኛው ደቂቃ ላይ ያደረጉም ሲሆን ነቢል ኑረዲን ያደረገውን ኢላማውን የጠበቀ የግብ ሙከራ ሞይስ ፓወቲ ግብ ከመሆን አድኖታል።

በቀላሉ ወደ አዳማ ከተማ የግብ ክልል ለመድረስ የተቸረጉት ፋሲል ከነማዎች በ22ኛው ደቂቃ ላይ ብሩክ አማኑኤል ከሳጥን ውጪ አክርሮ በመታው ኳስ ቀዳሚ ሙከራቸውን አድርገዋል።

በዘንድሮው የውድድር ዘመን የፋሲል ከነማ ጉዞ ጉልህ ሚና በመወጣት ላይ ከሚገኙት ተጫዋቾች መካከል ቀዳሚ የሆነው በረከት ግዛው ባጋጠመው ጉዳት በ24ኛው ደቂቃ ላይ ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል።

የስዩም ከበደው ቡድኑ የማጥቃት ብልጫውን ወስዶ በቀጠለባቸው ቀጣይ ደቂቃዎች ላይ በተለይም የቀኝ መስመር ተከላካዩ አብደልከሪም መሐመድ ወደ ሳጥን በሚያሻግራቸው ኳሶች ተደጋጋሚ ዕድሎችን ለመፍጠር ሲጥሩ ተስተውሏል።

በ27ኛው ደቂቃ ላይ አህመድ ሁሴን ከቢንያም አይተን የተቀበለውን ኳስ የፋሲል ከነማ ተከላካዮችን ሸውዶ በማለፍ ከሞይስ ፓወቲ ጋር ፊት ለፊት ቢገናኝም ኳስ እና መረብን ማገናኘት ሳይችል ቀርቷል።

በአጋማሹ ለዮሐንስ ሳህሌው ቡድን አስቆጪ በነበረው የግብ ሙከራ ያሬድ ብርሀኑ በረጅም የተላከለትን ኳስ ተቆጣጥሮ የግብ ጠባቂው አላዛር ማርቆስ መውጣትን ተከትሎ ከፍ አድርጎ ወደ ግብ የላከው ኳስ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል።

በ44ኛው ደቂቃ ላይ ሀይደር ሸረፋ ከቅጣት ምት ያሻገረውን ኳስ ነቢል ኑረዲን በግንባር ወደ ግብ ልኮ የግቡ አግዳሚ የመለሰበት እና በ45+1 ላይ ቢንያም አይተን ከግብ ጠባቂው ትይዩ ተገኝቶ ሳይጠቀምበት የቀሯቸው ኳሶች ለአዳማ ከተማዎች የአጋማሹ ሌሎች የግብ ዕድሎች የተፈጠሩባቸው አጋጣሚዎች ናቸው።

በሁለተኛው አጋማሽም የአዳማ ከተማ የማጥቃት እንቅስቃሴ ሲቀጥል በተለይም በግራ መስመር በኩል የፋሲል ከነማን የኋላ ክፍል ሰብረው ለመግባት ጥረቶችን አድርገዋል።

በፋሲል ከነማ በኩል በረጃጅም ኳሶች እና በሽግግር ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በመድረስ ለማጥቃት ያደረጓቸው ሙከራዎች በአጋማሹ ተስተውለዋል።

በሀዋሳ ከተማ ሳለ ከሳጥን ውጪ በሚያስቆጥራቸው ግቦች የሚታወቀው አቤኔዘር ዮሐንስ በ51ኛው ደቂቃ ላይ ከሳጥን ውጪ ያደረገው ጠንካራ የግብ ሙከራ ለጥቂት ከግቡ አግዳሚ በላይ ወጥቷል።

በጨዋታው 69ኛ ደቂቃ ላይ የአዳማ ከተማው የመሀል ተከላካይ መናፍ አወል ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ጨዋታውን አቋርጦ ወጥቷል።

በ71ኛው ደቂቃ ላይ ቃልኪዳን ዘላለም ከዳግም አወቀ የደረሰውን ግሩም ኳሶ ተጠቅሞ ግብ አስቆጠረ ተብሎ ሲጠበቅ ግብ ጠባቂው ቀድሞት ደርሶ ኳሱን አውጥቶታል።

በአዳማ ከተማ በኩል በአብዛኛው በግራ መስመር ያደላው የማጥቃት እንቅስቃሴ ይህ ነው ሊባል የሚችል ኢላማውን የጠበቀ የግብ ሙከራን ሳያስተናግድ ጨዋታው ተጠናቋል።

በ14ኛው ሳምንት ፋሲል ከነማ ከኢትዮጵያ ቡና እንዲሁም አዳማ ከተማ ደግሞ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ይጫወታሉ።

ከ10:00 ጀምሮ የተደረገው እና ቀዝቀዝ ያለ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ በታየበት ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ወልዋሎ አዲግራት ነጥብ ተጋርተዋል።

በቀዳሚው አጋማሽ ወልዋሎ አዲግራቶች ከተጋጣሚያቸው በተሻለ ወደ ሶስተኛው ዞን የሜዳ ክፍል መድረስ ቢችሉም ጠንካራ ሙከራዎችን ግን ማድረግ አልቻሉም።

በ34ኛው ደቂቃ ላይ ኮንኮኒ ሀፍዝ በሳጥን ውስጥ ያገኘውን ኳስ አክርሮ በመምታት ለጥቂት ወደ ውጪ የወጣበት በወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ በኩል የተመለከትነው ሙከራ ነበር።

በኢትዮ ኤሌክትሪክ በኩል ደግሞ በ42ኛው ደቂቃ ላይ ያሬድ የማነ ለግቡ ቅርብ ሆኖ ያገኘውን ኳስ ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ እንኳን ማድረግ ሳይችልበት ቀርቷል።

በሁለተኛው አጋማሽ ወልዋሎ አዲግራቶች በማጥቃት እንቅስቃሴ ተሽለው ቢቀጥሉም ከ65ኛው ደቂቃ በኋላ ኢትዮ ኤሌክትሪኮች ተጭነው ለመጫወት ችለዋል።

በተመሳሳይ ጠንካራ የግብ ሙከራዎች እምብዛም ባልነበሩት አጋማሹ ተቀይሮ የገባው እዮብ ገብረማርያም ከሳጥን ውጪ ያደረገው የ71ኛው ደቂቃ ከባድ ሙከራ በሙታክብዋ ጆኤል ተይዟል።

በወልዋሎ አዲግራት በኩል በ90+4ኛው ደቂቃ ላይ ጌትነት ተስፋዬ ያገኘውን አጋጣሚ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

በ14ኛው ሳምንት ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከተማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ደግሞ ከአዳማ ከተማ ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ አሰልጣኝ ውበቱና አሰልጣኝ በጸሎትን በልጧል…..
Next Article ሲዳማ ቡና መሪነቱን አላስነካም ብሏል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የ ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ጅማሮ እና ቁጥሮች !

kidus Yoftahe By kidus Yoftahe 5 years ago
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ 25ኛ ሳምንት ጨዋታ የቀጥታ ውጤት ማሳወቂያ
“መቶ ፐርሰንት ርግጠኛ ነኝ …እወዳደራለሁ” አቶ ገዛኸኝ ወልዴ
ጅማ አባጅፋር ከሀዲያ ሆሳዕና | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
ሻምፒዮኖቹ ሀድያ ሆሳእናን አሸነፋ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?