” ብዙ አልናገርም በሁለቱም ጨዋታዎች ተሸንፈናል በጨዋታዎቹ ዙሪያ ጥያቄ ካላችሁ ጠይቁኝ ”
” ለማጋነን ተብሎ 7ለ1 መባል የለበትም ክሬዲት ለማሳጣት እንዳይሆንባችሁ እሰጋለሁ 8 ለ 0 ተሸንፈንም እናውቃለን”
- ማሰታውቂያ -

ሽንፈቱን የአለም ፍጻሜ አታድርጉት ጊኒን የገጠምነው ትልቅ ቡድን ይዘን አይደለም የኡትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ይዘን ነው ” ሲል አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ ተናገረ።
ከጊኒ የደርሶመልስ የ7ለ1 ሽንፈት መልስ ዛሬ መግለጫ የሰጡት አሰልጣኙ ተጠባቂውን መግለጫ የጀመሩት ሁለቱን ጨዋታዎች አይታችኋል ብዬ ስለማመን ብዙ አልናገርም በሁለቱም ጨዋታዎች ተሸንፈናል በጨዋታዎቹ ዙሪያ ጥያቄ ካላችሁ ጠይቁኝ በማለት ለማብራራትም ፍላጎቱ ሳይኖራቸው የተጀመረ መግለጫ ሆየኗል።
የፊታችን ጥቅምት 23/2017 ስለሚጠናቀቀው
ውላተው የተጠየቁት አሰልጣኙ “ውሌ በ23 ይጠናቀቃል ያኔ እለቅላችኋለው ምን እንደሚያስጨንቃችሁ አላውቅም በ2 ጨዋታ 4ለ1 እና 3ለ0 ተሸነፍን እንጂ ለማጋነን ተብሎ 7ለ1 መባል የለበትም ክሬዲት ለማሳጣት እንዳይህንባችሁ እሰጋለሁ 8 ለ0 ተሸንፈንም እናውቃለን ሽንፈት ሲገጥም ከማንም በላይ ነው የምጎዳው ነገር ግን ተጨባጭ አቅማችንን ማወቅ አለብን ጊኒዎች ከ300 በላይ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች አሏቸው ሲገጥሙን የአቅማችን ልዩነት ታይቷል” ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
“በአሰልጣኝነት ህይወቴ ረጅም ጊዜ አልቆይም እስካለሁ ድረስ ግን አጨዋወቴን አልለውጥም
እንደ ቡድን ከጠየቃችሁኝ ተጨዋቾቻችን የተለያየ አቋም እያሳዩ መሆኑ ችግር ፈጥሮብናል ብዙዎቹ በአንድ ነገር ላይ መርካት ውስጥ ይገባሉ ሁለት ሶስት ጨዋታ ላይ በነበራቸው ጥሩ አቋም ላይ አይታዩም የፍሬዘርና የያሬድ አቋምም የሚያሳየው ይህንን ነው ከዲሞክራቲክ ኮንጎ ጋር በነበረን ጨዋታ ብዙ ስህተት የሰሩት እነሱ ናቸው” ያሉት አሰልጣኙ ባለሙያ አያስፈልገንም የሚል አቋም የለኝም ግን የስፒድ አሰልጣኝ ብናመጣም የተጫዋቾቻችን ፍጥነት በዚህ እድሜ አይሻሻልም” ሲል አስረድቷል።
” ዲሞክራቲክ ኮንጎን ሴራሊዮንና ጊኒንም የገጠምነው አዲስ አበባ ቢሆን ኖሮ በርግጠኝነነት እናሸንፍ ነበር ብሄራዊ ቡድኑ በሜዳው እንዲጫወት ጥረት ማድረግ አለባችሁ በአየራችንና በደጋፊዎቻችን እንዳንታገዝ አድርጎናል ይሄ ካልተለወጠ ችግር ነው” ሲል የመከረው አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ በርካታ ተጨዋቾችን ቀይሬያለሁ ምክንያቱ ደግሞ ተጨዋቾቼ ወጥ አቋም ስለማያሳዩ ነው በዚያ ላይ ኳስ ሲያገኙ ብቻ ነው የሚጫወቱት ይሄ ልክ አይደለም የኛ ስነልቦና ችግር እንዳለ ሆኖ አንድ ጎል ሲገባ ተጨማሪ ግብ ይገባብናል ይሄ በቀጣይ መታረም ያለበት ይሄ ትልቁ ችግራችን ነው” ብሏል።


