መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ መቐለ 70 እንደርታን በሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ ለማድረግ እየተሞከረ ነው…
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

መቐለ 70 እንደርታን በሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ ለማድረግ እየተሞከረ ነው…

አጋራ
አጋራ

 

በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ የሚሆነው የመቐለ 7 እንደርታን 4 ተጨዋቾችን ወደ አዲስ አበባ በማምጣት ክለቡን በውድድሩ ላይ እንዲቀጥል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተሰምቷል፡፡

ከዚህ መረጃ ጀርባ ካለው ምንጫችን በተገኘ መረጃ አራቱን ተጨዋቾች በትግራይ ክልል ባለው ጦርነት የተነሳ እስከ ሀሙስ እንደ 11ዱ ጓደኞቻቸው ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ከሆነ የካፍ ኤ ላይሰንስ ያለው አሰልጣኝ በጊዜያዊነት እንዲይዘው ተደርጎ አርብ ምሽት ወይም ቅዳሜ ጠዋት ካይሮ ለመብረር መታሰቡ ታውቋል፡፡

የመቐለ 70 እንደርታ ተጋጣሚ የሆነው የሊቢያው ክለብ ትሪፖሊ ላይ ጨዋታ ማድረግ ስለማይችል ቱኒዝ ላይ ይጫወትበት የነበረው ሜዳ ፋሲል ከነማ አርብ ምሽት የሚጫወትበት በመሆኑ በኤን ፒፒ አይ ሜዳ ጨዋታውን ለማድረግ መምረጡ ታውቋል፡፡ ከካፍና ከሊቢያው ክለብ ጋር ያለውን የመረጃ ልውውጥ የኢትዮጲያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በሃላፊነት እየተወጣ መሆኑ ታውቋል፡፡

አሁንም ግን የጉዞው ወጪ ከየት እንደሚመጣ የታወቀ ነገር የሌለ ሲሆን የካይሮ የቆይታ ሙሉ ወጪን ግን የሊቢያው ክለብ እንዲሸፍንና ከአንድ ሳምንት በኋላ በሚኖረው የመልስ ጨዋታ ላይ መቐለ 70 እንደርታ እንዲሸፍን ለማድረግ እየተሞከረ መሆኑ ታውቋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...