መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ ስድስት ተጨዋቾች ከመቐለ አዲስ አበባ ገቡ!
መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ስድስት ተጨዋቾች ከመቐለ አዲስ አበባ ገቡ!

አጋራ
አጋራ

 

*..የመቀለ 70 እንደርታ አመራሮች አያውቁም

በሀገር መከላከያ ሰራዊት ህግ የማስከበር ዘመቻ ምክንያት ጦርነት ውስጥ ያለችው መቐለ ለእግርኳስ ተጨዋቾች የምትመች ባትሆንም የመቐለ 70 እንደርታ ተጨዋቾች ግን በቀን ሁለቴ ልምምድ ሲሰሩ ሰንብተዋል እስከ ሰኞ ጠዋት ድረስ…. በተለምዶ ባሎኒ ሜዳ ከሚገኘው የማዘጋጃ ቤት ቢሮ አጠገብ የሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ውስጥ ያለውን አንደር ግራውንዱን ተፈላጊዎቹ የህወሀት ሰዎች ለስብሰባነት ለመጠቀም የገዳሙን አባቶችና አገልጋዮች በማስወጣት መሠብሠብ መጀመራቸውን የመከላከያ ሃይሉ መረጃ አግኝቶ በድሮን ጥቃት መሠንዘሩ ታውቋል፡፡

ይህን ተከትሎ የደህንነት ስሜት ያልተሰማቸው 6 የመቀለ 70 ተጨዋቾች ሰኞ ምሽት ተነስተው በሰመራ አፋር አድርገው ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ መግባታቸውን ከታማኝ ምንጭ የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ እነሱም አራ ቱ አፍሪካዊያን ኦኪኪ አፎላቢ… ዳንኤል ኦጄ..ሲሶኮና ካሉሺያ እንዲሁም ስዩም ተስፋዬና አሚን ነስሩ መሆናቸውም ታውቋል፡፡ ተጨዋቾቹ የክለቡ አመራሮች በተለይ ፕሬዝዳንቱ አቶ ሽፈራው ጋር ለመገናኘት ሞክረው አለመሳካቱ ታውቋል፡፡ ተጨዋቾቹ ከመቀለ ሲነሱም ሆነ አዲስ አበባ መግባታቸውን የክለቡ አመራሮች መረጃው የሌላቸው ሲሆን ለሻምፒየንስ ሊጉ ዝግጅት ሲባል በቀጣይ ጥቂት ቀናቶች ሌሎቹ ተጨዋቾች አዲስ አበባ ለዝግጅት እንዲመጡ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ምንጫችን ገልጿል፡፡

በቀጣይም የወልዋሎ አዲግራትና የስሁል ሽረ አባላትን ወደ አዲስ አበባ ለዝግጅት ለማምጣት ሙከራዎቹ ተጠናክረው ቀጥለዋል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...