በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ቅጣት የተጣለበት ተከላካይ ገንዘብ ላለመመለስ በሚል ከክለቡ ጋር ተለያይቷል።
ወደ ኢትዮጵያ ከመጣ አምስት አመታት አልፎታል። የሀገሩን ክለብ ሌቨርቲ ፕሮፌሽናልን ለቆ ቅዱስ ጊዮርጊስ በመቀላቀል ከክለቡ ጋር የተሳኩ ጊዜያትን በማሳለፍ የሊጉን ዋንጫ ከፍ አድርጎ ማንሳት የቻለ ሲሆን በ2017 ወደ ሌላኛው የሊጉ ክለብ መቻል በማምራት ክለቡን በሁለት አመት ውል መቀላቀል ችሏል።
የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር የፋይናንስ ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ያስቀመጥኩትን የገንዘብ አከፋፈል ህግ አልተከተልም በሚል በተለያዩ ክለቦች እና ተጫዋቾች ላይ ቅጣትን ሲያስተላልፍ ጋናዊው የመሐል ተከላካይ ፍሪምፓንግ ሜንሱ ግን አሻፈረኝ በሚል ከሦስት ሚሊዮን ብር በላይ መመለስ ያለበትን ብር ተፈፃሚ አላደርግም በሚል ከጦሩ ጋር በስምምነት ተለያይቶ ወደ ሀገሩ አምርቷል። ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ተጫዋቾች ቅጣታቸውን ተፈፃሚ እያደረጉ ባሉበት በአሁኑ ወቅት ይህ ጋናዊ ተከላካይ ግን ቅጣቱን ተግባራዊ ሳያደርግ ወደ ጋና አምርቶ የቀድሞው ክለቡ አሻንቲ ኮቶኮን ሊቀላቀል እንደሚችልም ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።



