By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ሪፖርት | መድን ፣ ሸገር እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን ረተዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስሀዋሳ ከተማመቐለ 70 እንደርታሀዲያ ሆሳዕናየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሪፖርት | መድን ፣ ሸገር እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን ረተዋል

hatricksport team
hatricksport team 4 months ago
Share
SHARE

በአራተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን መርሀ-ግብር ኢትዮጵያ መድን እና ሸገር ከተማ የመጀመሪያ ድላቸውን ሲያሳኩ ሀዋሳ ከተማ ደግሞ ሦስተኛውን የዓመቱ ድሉን አስመዝግቧል።

ሀድያ ሆሳዕና 1-2 ኢትዮጵያ መድን

ከቀትር መልስ ከአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታዎቹን ጨርሶ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር ጨዋታውን ያደረገው ኢትዮጵያ መድን የሊጉን የመጀመሪያ ድል በስኬት ቋጭቷል። ተመጣጣኝ አጀማመር የነበረው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በተሻለ እንቅስቃሴ ሁሉቱም መጫወት መርጠው ቢታዩም ኳስ እና መረብን በማገናኘቱ ግን መድኖች የበላይ ነበሩ። 28ኛው ደቂቃ ላይ ከግራ መስመር ያሬድ ካሳዬ ያሻማለትን ኳሶ ረመዳን የሱፍ ገጭቶ የግብ ዘቡ ያሬድ ካሳዬ በአግባቡ መቆጣጠር ያልቻላትን ኳስ ዩጋንዳዊው አጥቂ አለን ካይዋ ወደ ጎልነት በመለወጥ ቡድኑን መሪ አድርጓል።

ጎልን ካስተናገዱ በኋላ በይበልጥ ፈጣን ሽግግርን ሲጠቀሙ የተስዋሉት ሀድያ ሆሳዕናዎች ወደ ጨዋታ የመለሳቸውን ግብ በአጋማሹ ጭማሪ ደቂቃ 45+1 ላይ አስቆጥረዋል። በመልሶ ማጥቃት ከብሩክ በየነ በአግባቡ መሬት ለመሬት የተሰጠውን ኳስ ፈጣኑ የመስመር አጥቂ ተመስገን ብርሀኑ ፋሲል ገብረሚካኤል መረብ ላይ አሳርፎ ቡድኑን ወደ አቻነት አምጥቷል።

- ማሰታውቂያ -

ከዕረፍት መልስ ከመጀመሪያዎ አኳያ ወረድ ያሉ ፉክክሮች በተንፀባረቁበት አጋማሽ ቡድኖች ከመረጡት የጨዋታ እንቅስቃሴ በቀር የተለየ የማጥቃት ሁነትን ማስመልከት ባይችሉም መድኖች ግን የአሸናፊነት ጎልን ማግኘት ችለዋል። መደበኛው የጨዋታ ደቂቃ ሊጠናቀቅ አንድ ደቂቃ ብቻ ሲቀረው አማኑኤል ኤርቦ ወደ ሳጥን ያሻማትን ኳስ ለማውጣት ጥረት ሲያደርግ የነበረው ዳግም ንጉሴ በራሱ መረብ ላይ በማስቆጠር ጨዋታው በመጨረሻም በኢትዮጵያ መድን 2ለ1 አሸናፊ ተገባዷል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ 0-1 ሸገር ከተማ

የአዲስ አበባ ስታዲየም ሁለተኛው ጨዋታ አስር ሰዓት ሲል ጊዮርጊስ እና ሸገር ከተማን ያገናኘው ጨዋታ ሸገር ከተማ የሊጉን የመጀመሪያ ድል ያገኘበትን ውጤት አስመዝግቧል። ሜዳ ላይ ቡድኖች መርጠው ለመጫወት ከሞከሯቸው እንቅስቃሴዎች ውጪ ብዙም የጠሩ አጋጣሚዎች ባልነበሩት ጨዋታ ከመጀመሪያው አጋማሽ ይልቅ ሁለተኛው አጋማሽ በተሻለ መነቃቃቶችን ያሳየን ቢመስልም በግብ ሙከራዎች መድመቅ ላይ ግን አሁንም ደካማ ነበር።

ይሁን እንጂ ከዕረፍት መልስ ፈጣን አጀማመር የነበራቸው ሸገር ከተማዎች 47ኛው ደቂቃ ሔኖክ አዱኛ ከቅጣት ያሻገረልን ኳስ ከከፍተኛ ሊጉ ቡድኑን ያሳደገው ያሬድ መኮንን ዘደ ጎልነት ለውጦ ቡድኑን መሪ አድርጓል። መሪነታቸው ካወቁ በኋላ በቢኒያም ፍቅሬ እና አቤል ያለው በሚመራው የአጥቂ ክፍል በድግግሞሽ ፈረሰኞቹ ሲያጠቁ ቢታይም የተለየ ነገርን ማድረግ ሳይችሉ የሊጉን የመጀመሪያ ሽንፈት ሸገሮች በበኩላቸው የመጀመሪያ ድላቸው አስመዝግበውበት ተቋጭቷል።

መቐለ 70 እንደርታ 1-3 ሀዋሳ ከተማ

በጨዋታው የመጀመሪያዎቹ አስር ደቂቃዎች አጀማመራቸውን ፈጠን ባሉ ቅብብሎች በማድረግ በእንቅስቃሴ ብልጫን ለመያዝ ጥረት ያደረጉት ሀዋሳዎች ጎል ያስቆጠሩት ገና በጊዜ ነበር። 8ኛው ደቂቃ ያሬድ ብሩክ ወደ ግራ ካደላ ቦታ ወደ ጎል ሞክሮ ግብ ጠባቂው ሶፎኒያስ ሠይፈ የተፋትን ኳስ ልማደኛው አጥቂ ጌታነህ ከበደ በቀላሉ መረቡ ላይ አሳርፎ ሐይቆቹን ቀዳሚ አድርጓል። በወጣቱ የመስመር ተከላካይ የአብስራ ደግፌ ሁለት ሙከራዎችን ካደረጉ በኋላ በእንቅስቃሴ በተጋጣሚያቸው ለመበለጥ የተገደደው የአሰልጣኝ ተመስገን ዳናው ሀዋሳ ከተማ 24ኛው ደቂቃ ላይ ሱለይማን ሀሚድ ግሩም የቅጣት ምት ጎል አክሎ መቐለን ወደ 1ለ1 ማሸጋገር ችሏል። ወደ ጨዋታ የሚመልሳቸው ጎል ካገኙ በኋላ በይበልጥ ጨዋታውን መቆጣጠር የቻሉት እና በኪቲካ ጀማ እና ፍፁም አለሙ አማካኝነት መሪ ሊያደርጋቸው የሚችላቸውን አጋጣሚዎችን መቐለዎች ማግኘት ቢችሉም ወደ ግብነት መለወጥ ሳይችሉ ቀርዋል።

ከዕረፍት መልስ የተጫዋቾችን ቅያሪ በማድረግ ወደ ሜዳ የተመለሱት ሀዋሳዎች በድጋሚ መሪ ሆነዋል። 47ኛው ደቂቃ ላይ ቢኒያም በላይ ከዘረሰናይ ብርሀነ የነጠቀውን ኳስ ወደ ሳጥን ሲያሻግር ያሬድ ብሩክ ለቡድኑ ሁለተኛ ለራሱ የውድድር ዘመኑ ሦስተኛውን ጎል አስቆጥሯል። ጨዋታው ቀጥሎ መቐለዎች በእንቅስቃሴ የበላይነቱን ቢወስዱም ሱለይማን ሀሚድ እና አሸናፊ ሀፍቱ ካደረጓቸው ቀላል ሙከራዎች ውጪ የመጨረሻው ሜዳ ላይ ኮስታራ መሆን አለመቻላቸውን ተከትሎ በ84ኛው ደቂቃ የመቐለው ተከላካይ ፍሬዘር ካሳ ከዕለቱ ዋና ዳኛ ኤፍሬም ደበሌ ጋር በፈጠረው ሰጣገባ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ተወግዷል። በተቃራኒው ጨዋታው ሊገባደድ 89ኛው ደቂቃ ተጨማሪ ጎልን ለማስተናገድ ተገደዋል።  ጌታነህ ከበደ ከሳጥኑ ጠርዝ አካባቢ የተገኘን የቅጣት ምት አክርሮ መቶ መረቡ ላይ አስቀምጦ ለራሱ ሁለተኛ የውድድር ዘመኑ አራተኛ ጎሉ አድርጎ በ90+3ኛው የሀዋሳ ከተማው ተከላካይ በረከት ሳሙኤል በሰራው ጥፋት በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ወጥቷል። ጨዋታው በሀዋሳ ከተማ 3ለ1 ድል አድራጊነት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By hatricksport team
Follow:
Hatricksport team
Previous Article ጋናዊው ተከላካይ የቅጣት ገንዘብ ላለመክፈል ከመቻል ጋር ተለያየ
Next Article የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ባሳለፍነው ሳምንት በ ሁለት ከተሞች ጅማሮዉን አደረገ !

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎች

“ዳኝነቱ ጥሩ ነበር፤ ፍፁም ቅጣት ምቱም ያሰጣል፤ጊዮርጊስን ማሸነፍ ይገባን ነበር” ሱራፌል ዳኛቸው (ፋሲል ከነማ)

መሸሻ ወልዴ By መሸሻ ወልዴ 6 years ago
የሉሲዎቹ አዲሱ ዋና አሰልጣኝ ታውቋል
ዝውውር| ወልዋሎ ዓ.ዩ ተስፋይ ዲባባ ከድሬዳዋ ከተማና አራት አዳዲስ ተጫዋቾች ሲያስፈርም የአንድ ተጫዋች ውል ዛሬ ማራዘሙን አሳውቋል 
ኢንተርናሽናል አርቢትር ባምላክ ተሰማ የመራው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ዋልያዎቹ በፊፋ ወርሀዊ ደረጃ አንድ ደረጃ ከፍ ብለዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?