መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ | ወልቂጤ ከተማ ከመመራት ተነስተው ከኢትዮጵያ ቡና ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡናወልቂጤ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጨዋታ ዘገባ | ወልቂጤ ከተማ ከመመራት ተነስተው ከኢትዮጵያ ቡና ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል

አጋራ
አጋራ

 

በአንደኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ትላንት መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን ዛሬ ደግሞ ከረፋዱ አራት ስአት ላይ ኢትዮጵያ ቡናን እና በወልቂጤ ከተማን ያገናኘው ጨዋታ ክትፎዎቹ ከመምራት ተነስተው ነጥብን ተጋርተው 2-2 በሆነ ውጤት ተለያይተዋል።

ሁለቱም ቡድኖች ኳስን ተቆጣጥረው ለመጫወት ሲታትሩ የተስተዋለ ሲሆን በተለይም ከግብ ጠባቂ ጀምረው ወደ ፊት ለማጥቃት የሞከሩት ቡናማዎቹ በመጀመሪያው አጋማሽ ብልጫ ነበራቸው። ከግብ ጠባቂ ኳስ ለመመስረት ፍላጎት የነበራቸው ቡናማዎቹ በተለይ ግብ ጠባቂው አቤል ማሞ ለቡድን አጋሮቹ በማቀበል ላይ ተደጋጋሚ ስህተቶች ተስተውሎበት ተመልክተናል። በዚህም አህመድ ሁሴን አቤል ማሞ ለአበበ ጥላሁን አቀብላለው ሲል በፈጠረው ስህተት አገባው ሲባል ለጥቂት በቋሚው የወጣችበት ወልቂጤ ከተማን መሪ ማድረግ የምትችል ነበረች።

ቡናማዎቹ በበኩላቸው በጥሩ ቅብብል የተገኘችውን ኳስ ፍቅረየሱስ ተክለብርሀን ሲሞክር ጀማል ጣሰው በቀላሉ ተቆጣጥሮበታል። የመጀመሪያውን አጋማሽ ምንም ግብ ሳይስተናገድበት 0-0 በሆነ ውጤተ ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

በሁለተኛው አጋማሽ ብልጫቸውን የተጠቀሙት ኢትዮጵያ ቡናዎች ቀዳሚ መሆን ችለዋል። አቡበከር ናስር በራሱ ላይ በተሰራው ጥፋት የተገኘችውን የፍፁም ቅጣት ምት በቀላሉ ማስቆጠር ችሏል። በመልሶ ማጥቃት አቡበከር ናስር እና ታፈሰ ሰለሞን ተቀባብለው ጀማል ጣሰው ያመከናት ኳስ አስቆጪ ነበረች። እንዳለ ደባልቄ የወልቂጤ ከተማዎች የኳስ ቅብብል ስህተት ተጠቅሞ ያገኛትን ኳስ ለአቡበክር ናስር አቀብሎት በሚገባ ተጠቅሞ ለራሱ እና ለቡድኑ ሁለተኛ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

ከግቦቹ መቆጠር በኋላ ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ወደ ጨዋታ ቅኝት መግባት የቻሉት ክትፎዎቹ በያሬድ ታደሰ አማካኝነት ግብ አስቆጥረው ልዩነቱን ማጥበብ ችለዋል። የመከላከል ችግር በጉልህ ሲታይባቸው የነበሩት ቡናማዎቹ ግብ ከማስተናገድ አላዳናቸውም። በዚህም የኢትዮጵያ ቡናን ተከላካዮች ስህተት በሚገባ የተጠቀመው ረመዳን ናስር ቡድኑን አቻ የምታደርግ ግብ አስቆጥሮ ነጥብ ተጋርተው እንዲወጡ አስችሏል። ጨዋታው 2-2 አቻ በሆነ ውጤት መጠናቀቅ ችሏል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...