መነሻ ገጽ ባህርዳር ከተማ የጨዋታ ዘገባ | ክትፎዎቹ አሸናፊነታቸውን አስቀጥለዋል
ባህርዳር ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግወልቂጤ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ክትፎዎቹ አሸናፊነታቸውን አስቀጥለዋል

አጋራ
አጋራ

 

በአራተኛው ሳምንት የመጨረሻ ቀን መርሀ ግብር ወልቂጤ ከተማን ከ ባህርዳር ሲያገናኝ ክትፎዎቹ አሸናፊነታቸውን ያስቀጠሉበትን ውጤት ይዘው ለመውጣት ችለዋል ።

ወልቂጤ ከተማዎች ብልጫ በወሰዱበት የመጀመሪያ አጋማሽ በተለይም በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ የጎል ሙከራዎችን ሲያደርጉ ተስተውለዋል ።ክትፎዎቹ በተለይም ከቆሙ ኳሶች አስደንጋጭ ሙከራን ሲያደርጉ መሪ የሆኑበትን ጎልም ከዚህ የጨዋታ እንቅስቃሴ ማግኘት ችለዋል ።

ወልቂጤ ከተማዎች በተስፈኛው ታዳጊያቸው ያሬድ ታደሰ የቅጣት ምት ሙከራ አስደንጋጭ ሙከራን ሲያደርጉ ሀሪሰን ሄሱ አልፎም የግቡ ቋሚ ሊመልሱበት ችለዋል ። ክትፎዎቹ መሪ ያደረገችውን ግብ ፍሬው ሰለሞን ከቅጣት ምት ያሻማውን ቶማስ ስምረቱ ከመረብ በማሳረፍ መሪ ሊያደርጋቸው ችሏል ።

 

የጣና ሞገዶቹ እምብዛም የግብ ዕድል ባለፈጠሩበት እና ተቀዛቅዘው በታዩበት የመጀመሪያው አጋማሽ ከማዕዘን ምት ከተሻገረችው የግብ ዕድል እና የግቡ አግዳሚ ከመለሰው ውጪ አስደንጋጭ ሙከራን ማድረግ ሳይችሉ የመጀመሪያው አጋማሽ ሊጠናቀቅ ችሏል ።

በሁለተኛው አጋማሽ ሁለቱም ቡድኖች መጠነኛ ፉክክርን ለማድረግ ሲሞክሩ በተለይም ባህርዳር ከተማዎች የሚያስቆጩ የግብ ዕድሎች ከሽፈውባቸዋል ። በተቃራኒው ወልቂጤ ከተማ ውጤቱን አስጠብቀው ለመውጣት በመልሶ ማጥቃት የግብ እድሎችን ለመፍጠር ሲሞክሩ በጨዋታው ሂደት አልሳሪ አልመሀዲን በቀይ ካርድ ለማጣት ተገደዋል ።

ባህር ዳር ከተማዎች በሁለተኛው አጋጓሽ ተጭነው ለመጫወት ሲሞክሩ ግርማ ደሲሳ ያሻማውን ኳስ ፍፁም አለሙ የሞከረው እንዲሁም ባዬ ገዛኸኝ ከሳጥን ውጪ አክርሮ ወደ ግብ የሞከረውን ኳስ ጀማል ጣሳው ያወጣባቸው አጋጣሚዎች ለጣና ሞገዶቹ ለግብ የቀረቡ እድሎች ነበሩ ።

በመከላከሉ ላይ ተጠምደው የቆዩት ወልቂጤ ከተማዎች ተሳክቶላቸው ውጤቱን አስጠበቀው ሲወጡ በአራት ሳምንት የሊጉ ጨዋታዎች ላይ ሽንፈትን ሳያስተናግዱ ቀርተዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...