መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ የጨዋታ ዘገባ | ሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል
ሀዋሳ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል

አጋራ
አጋራ

 

በአራተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሁለተኛ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡናን ከ ሀዋሳ ከተማ ሲያገናኝ በሀዋሳ ከተማ አሸናፊነት ሊጠናቀቅ ችሏል ።

የመጀመሪያው አጋማሽ በጥቅሉ በ ኢትዮጵያ ቡና የኳስ ቁጥጥር የበላይነት እና አስደንጋጭ ሙከራዎች ሁለቱም ቡድኖች ሳያደርጉበት ሲጠናቀቅ ቡናማዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ ኳስን ከኋላ መስርቶ ለመውጣት በሚያደርጉት ጊዜ በመልሶ ማጥቃት ሙከራዎች ሲደረጉባቸው ተስተውሏል ።

ኢትዮጵያ ቡናዎች በመጀመሪያው አጋማሽ የመጀመሪያዎቹ ደቂቃ ላይ አቤል ከበደ ከመስመር ያሻገረውን ኳስ ሀብታሙ ታደሰ ሞክሮት ግብ ጠባቂው ሰሆሆ ሜንሳህ ካዳነበት የሚያስቆጭ ሙከራ ውጪ አስደንጋጭ የሚባልን ሙከራን ሳያደርጉ ለመውጣት ችለዋል ።

ሀዋሳ ከተማዎች በተቃራኒው አልፎ አልፎ በሚያገኙት እድሎች ወደ ግብ ሲቀርቡ ወንድማገኝ የሞከረው እና በቀኝ የግብ አግዳሚ ታካ የወጣችው ኳስ ቀዳሚው ሙከራቸው ነበረች ። ከዚህ ሙከራ በኋላ ወደ ግብ ዳግም መድረስ የቻሉት ሀዋሳ ከተማዎች ዘነበ ከነደ ከመስመር ያሻገረውን ኳስ ብሩክ በየነ በደረቱ አብርዶ ቢሞክረም በቀላሉ ተክለማርያም ሻንቆ ሊቆጣጠረው ችሏል ።

 

የመጀመሪያው አጋማሽ ያን ያህል የግብ እድልን ሳያሳይ ሲጠናቀቅ በሁለተኛው አጋማሽ ጅማሮ ላይ ተመሳሳይ የጨዋታ እንቅስቃሴን ለመመልከት ተችሏል ። ሀዋሳ ከተማዎች በሁለተኛወረ አጋማሽ የማጥቃት አማራጫቸውን ኤፍሬም አሻሞን በማስገባት የማጥቃት ጫናዎችን ለማሳደር ሲሞክሩ ፍሬ አፍርቶላቸው የኢትዮጵያ ቡና ግብ ጠባቂ ተክለማርያም ሻንቆ መሳሳትን ተከትሎ ብሩክ በየነ ሀዋሳ ከተማን ቀዳሚ ማድረግ ችሏል ።

ከግቡ መቆጠር በኋላ ሀዋሳ ከተማዎች በተመሳሳይ የጨዋታ እንቅስቃሴ በረጃጅም ኳስ ለብሩክ በየነ በሚጣሉ ኳሶች የግብ እድሎችን መፍጠር ቢችሉም ከሙከራነት መዝለል አልቻሉም ። ቡናማዎቹ ከመጀመሪያው አጋማሽ ይበልጥኑ በተቀዛቀዙበት የጨዋታ እንቅስቃሴ አብበከር ናስር ከቋሞ ኳስ ተሻግሮለት ከወጣችበት የግብ ሙከራ ውጪ አስደንጋጭ ወይም ለግብ የቀረበ ሙከራን ማድረግ ሳይችሉ ጨዋታው ተጠናቋል ።

ኢትዮጵያ ቡና የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ሽንፈት ሲያስተናግዱ አሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት የመጀመሪያ ድላቸውን ከቡናማዎቹ ላይ ሶስት ነጥብ በመውሰድ ማሳካት ችለዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...