በኢትዮጵያ ዋንጫ የአራተኛ ቀን መርሀግብር የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ወደ ግማሽ ፍፃሜው ነገሌ አርሲን በመርታት ማለፉን አረጋግጧል።

በአዲስ አበባ ስታዲየም ሁለቱን የፕሪምየር ሊጉን ጠንካራ ክለቦች በአራተኛ ቀን ያገናኘው የኢትዮጵያ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ መርሀግብር ሲዳማ ቡና 2ለ1 በሆነ ውጤት ነገሌ አርሲን በመርታት ወደ ግማሽ ፍፃሜው አልፏል። በመጀመሪያው አጋማሽ ክለቡን ከተቀላቀለ በኋላ በድንቅ ብቃቱ ላይ የሚገኘው አቤል ያለው 22ኛው ደቂቃ ላይ የነገሌ አርሲው ተከላካይ ሮሆቦት ሰላሎ በሰራው ስሆተት የተገኘችዋን አጋጣሚ ወደ ጎልነት ሲለውጥ ከዕረፍት መልስ ኪቲካ ጀማ ተቀይሮ ከገባ በኋላ እንደነበረው ጥሩ አበርክቶ 63ኛው ደቂቃ የሲዳማ ቡናው የግብ ዘብ አላዛር መርኔ በሰራው ስህተት ያገኛትን አጋጣሚ ወደ ጎልነት ለውጦ ነገሌን አቻ ቢያደርግም 76ኛው ደቂቃ ላይ አቤል ያለው አስጀምሮ ሱራፌል ዳኛቸው ያመቻቸለትን ኳስ ዮሴፍ ዮሐንስ ከሳጥን ውጪ አስደናቂ ጎልን በማስቆጠር ጨዋታው በሲዳማ ቡና 2ለ1 አሸናፊነት ተቋጭቷል።
በግማሽ ፍፃሜው ሲዳማ ቡና ከ ወልዋሎ አዲግራት ጋር እንደሚገናኝም ይጠበቃል።
አስተያየት ይስጡ