መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ አዳማ ከተማን ረተዋል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአዳማ ከተማዜናዎችፋሲል ከነማ

የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ አዳማ ከተማን ረተዋል

አጋራ
አጋራ

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ውሎ ቀዳሚ ጨዋታ ፋሲል ከነማን ከአዳማ ከተማ አገናኝቶ በፋሲል ከተማ አሸናፊነት የ2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል ።

በአሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽ የሚመሩት ፋሲል ከነማዎች በቋሚ አሰላለፍ ሚካኤል ሳማኪ ፤ አምሳሉ ጥላሁን ፤ ከድር ኩሊባሊ ፤ አስቻለው ታመነ ፤ ዓለምብርሀን ይግዛው ፤ ሽመክት ጉግሳ ፤ በዛብህ መለዮ ፤ ይሁን እንደሻው ፤ ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ ፤ ሀብታሙ ገዛኸኝ እና ፍቃዱ አለሙ የተሰለፉ ሲሆን በአሰልጣኝ ይታገሱ እንዳሉ በሚመሩት አዳማ ከተማ በኩል ደግሞ ሰይድ ሀብታሙ ፤ ጀሚል ያዕቆብ ፤ ሚሊዮን ሰለሞን ፤ አዲስ ተስፋዬ ፤ ደስታ ዮሀንስ ፤ አማኑኤል ጎበና ፤ መስዑድ መሐመድ ፤ ዊሊያም ሰለሞን ፤ ዳዋ ሆጤሳ ፤ አብዲሳ ጀማል ፤ እና አሜ መሐመድ በቋሚ አስራአንድ የተሰለፉ ተጫዋቾች ናቸው ።

የቀትሩ ጨዋታ በሁለቱም በኩል በሁለቱም በኩል ቶሎ ቶሎ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ ፍላጎት በታየበት የጨዋታ እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን በ14 ደቂቃዎች ውስጥም ሁለት ግቦች ተስተናግደውበታል ።

በቀጥተኛ አጨዋወት ወደ ግብ የመድረስ አዝማሚያዎች በተስተዋሉበት ጨዋታ አፄዎቹ በ8ኛው ደቂቃ ላይ ቀዳሚ መሆን የቻሉበትን ግብ አስቆጥረዋል ። የፋሲል ከነማን የፊት መስመር የሚመራው ፍቃዱ አለሙ ከሽመክት ጉግሳ በተከላካዮች መካከል የደረሰውን ኳስ በአዳማ ከተማ መረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል ።

ነገር ግን የአፄዎቹ መሪነት ከስድስት ደቂቃዎች በላይ የዘለቀ አልነበረም ። በግሩም ቅብብል በሳጥኑ የግራ አቅጣጫ ይዘው የገቡትን ኳስ በአንጋፋው ተጫዋች መስዑድ መሐመድ አቀባይነት በአሜ መሐመድ ጨራሽነት አዳማ ከተማዎች አቻ የሆኑበትን ግብ አስቆጥረዋውል ።

የአዳማ ከተማዎች ደስታ እየገለፁ ባሉበት ቅፅበት ግን የመሀል ክፍል ተጫዋቻቸው ዊልያም ሰለሞን በሁለተኛ የቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል ።

ምንም እንኳን አዳማ ከተማዎች የቁጥር ብልጫ ቢወስደባቸውም በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ይየ ሁለተኛ ግብ ለማስቆጠር የአፄዎቹን የኋላ መስመር ለመፈተን ጥረቶችን አድርገዋል ።

ቀስ በቀስ ፋሲል ከነማዎች በኳስ ቁጥጥሩ ብልጫ ወስደው በመጫወት ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ የቻሉባቸውን አጋጣሚዎች መፍጠር ቢችሉም የአዳማ ከተማን የኋላ መስመር አልፈው ግብ ለማስቆጠር አልቻሉም ነበር ።

የመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜም በአንድ አቻ ውጤት ተጠናቋል ።

በሁለተኛው አጋማሽ ፋሲል ከነማዎች በተሻለ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ከተጋጣሚያቸው በተሻለ በመንቀሳቀስ መጫወት የቻሉ ሲሆን በዚህም በ53ኛው ደቂቃ ላይ ዳግም መሪ የሆኑበትን ግብ አግኝተዋል ።

ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ በግራ መስመር አቅጣጫ ከአምሳሉ ጥላሁን የተቀበለውን ኳስ በግሩም ሁኔታ የአዳማ ከተማ ተከላካዮችን አልፎ ለፍቃዱ አለሙ ያቀበለው ኳስን አጥቂው ለራሱ እና ለክለቡ ሁለተኛ ግብ አድርጎ አስቆጥሯል ።

የቁጥር ብልጫ የነበራቸው አፄዎቹ በተሻለ እንቅስቃሴ ሶስተኛ ግብ ለማከል በሚጫወቱበት ሰዓት በነሱም በኩል ሽመክት ጉግሳ በ68ኛው ደቂቃ ላይ በሁለተኛ የቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል ።

በጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ አዳማ ከተማዎች ተጭነው በመጫወት የግብ ዕድል ለመፍጠር ያደረጓቸው ጥረቶች ሳይሰምሩ ጨዋታው በፋሲል ከነማ አሸናፊነት ተጠናቋል ።

በሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው መስከረም 27 አርብ 10:00 ላይ አዳማ ከተማ ከመቻል ሲጫወት ፋሲል ከነማ በበኩሉ ባለበት የኮንፌዴሬሽን ካፕ ጨዋታ ምክንያት ከድቻ የሚያደርገውን የሁለተኛ ሳምንት ጨዋታ ህዳር 27 10:00 ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ያደርጋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...