መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ | ወልቂጤ ከተማ በጌታነህ ከበደ ብቸኛ ግብ ሶስት ነጥብ አግኝቷል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአዲስአበባ ከተማወልቂጤ ከተማየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ወልቂጤ ከተማ በጌታነህ ከበደ ብቸኛ ግብ ሶስት ነጥብ አግኝቷል

አጋራ
አጋራ

የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሰባተኛ ሳምንት የመጀመሪያ ጨዋታ አሰልጣኙን ካሰናበተ በኋላ በተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ጥሩ ውጤቶችን ይዞ እየወጣ ያለውን አዲስ አበባ ከተማን በአሰልጣኝ ጳውሎስ ጌታቸው ከሚመራው ወልቂጤ ከተማ ጋር አገናኝቶ የመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ላይ የብሄራዊ ቡድኑ አጥቂ ጌታነህ ከበደ ባስቆጠረው ብቸኛ ግብ ወልቂጤ ከተማ 1 ለ 0 አሸንፎ ወቷል ።

አዲስ አበባ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን ባሸነፉበት ጨዋታ ከተጠቀሙት ቋሚ አሰላለፍ አንድ ቅያሪ ብቻ በማድረግ ብዙአየሁ ሰይፉን ወደ ጨዋታው ሲያስገቡ በወልቂጤ ከተማ በኩል ደግሞ በስድስተኛው ሳምንት ከተጠቀሙት ቋሚ 11 ስድስት ያህል ቅያሪዎችን በማድረግ ሀብታሙ ሸዋለም ፤ ተስፋዬ ነጋሽ ፤ በሀይሉ ተሻገር ፤ ዮናስ በርታ ፤ ያሬድ ታደሰ እና እስራኤል እሸቱን ጨዋታውን እንዲጀምሩ አድርገዋል ።

በጨዋታው በሁለቱም በኩል ወደ በቀጥተኛ አጨዋወት ወደ ፊት ለመሄድ ሙከራዎችነሰ አድርገዋል ። አዲስ አበባ ከተማዎች በፈጣን ቅብብል ወደ ጎሎች ለመድረስ ሲሞክሩ በወልቂጤ ከተማ በኩል ረጃጅም ኳሶችን የመጠቀም ሁነቶች ተመልክተናል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ ዕድል ያገኙት ወልቂጤ ከተማዎቾ የነበሩ ሲሆን ተስፋዬ ነጋሽ በረጅም የተላከለትን ኳስ ተከላካዮችን በፍጥነት አልፎ ያገኘውም ቢሆንም ፊት ለፊቱ ለመጣበትን ግብ ጠባቂን በአየር ላይ ለማሳለፍ ሲሞክር ኳሱ በመርዘሙ ወደ ውጪ ወቶበታል ። በአዲስ አበባ ከተማ በኩል 5ኛው ደቂቃ ላይ እንዳለ ከበደ ለፍፁም ጥላሁን በሳጥን ውስጥ ጥሩ ኳስ ቢያቀብለውም ፍፁም ሳይደርስበት ቀርቷል ።

በተከታዮቹ ደቂቃዎች በብዛት ቶሎ ቶሎ የመቀማማት እና አንድ ቡድን ኳሱን ይዞ ጫና ማሳደር ያልቻለበት ነበር ። ነገር ግን የመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ጨዋታው ፈጠን ብሎ የግብ ዕድሎች የታዩበት ነበር ። 41ኛ ደቂቃ ላይ ፍፁም አለሙ ከመሀል ክፍል የደረሰውን ኳስ ረመዳን የሱፍን አልፎ ከፊቱ የነበረው አበባው ቡጣቆም ወድቆለት ከግብ ጠባቂው ጋር ቢገናኝም በማይታመን ሁኔታ የመታው ኳስ ወደ ውጪ ወቷል ። ከአራት ደቂቃዎች በኋላ ወልቂጤ ከተማዎቾ ያገኙትን የቅጣት ምት ሀብታሙ ሸዋለም ወደ ግብ ሲያሻማው በአዲስ አበባ ተከላካዮች ስህተት ነፃ የነበረው ጌታነህ ከበደ በግንባሩ ገጭቶ አስቆጠረው ።

በሁለተኛው አጋማሽ በስፋት አዲስ አበባ ከተማዎቾ ቅያሪዎችን በማድረግ ውጤቱን ለመቀልበስ የሞከሩበት ነበር ። 54ኛው ደቂቃ ላይ ከማዕዘን የተነሳውን ኳስ ሳሙኤል ተስፋዬ ከሳጥን ውጪ አክርሮ ወደ ግብ የመታው ኳስ በሲልቭያን ግቦሆ ተመልሶ የማዕዘን ምት ሆኗል ። አዲስ አበባ ከተማዎች ጫና አሳድረው ግብ ለማግኘት ሙከራዎቻቸወን የቀጠሉ ሲሆን በወልቂጤ ከተማ አልፎ አልፎ ወደ ፊት በመሄድ ጥረቶችን ማድረግ ችለዋል ።

63ኛ ደቂቃ ላይ ጌታነህ ከበደ ከአዲስ አበባው ተከላካይ ሳሙኤል የነጠቀውን ኳስ ለአብዱልከሪም ወርቁ አቀብሎት አብዱልከሪም ጠንከር አድርጎ ሳይመታው ዳንኤት ተሾመ በቀላሉ ይዞታል ። በቀሪዎቹ ደቂቃዎች ጨዋታው ቀዝቀዝ ብሎ ቀጥሎ ሌላ ተጨማሪ ግብ ሳያስተናግድ በወልቂጤ ከተማ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል ።

ውጤቱን ተከትሎም አዲስ አበባ ከተማ በ10 ነጥብ ባለበት 5ኛ ደረጃ ላይ የሚቆይ ሲሆን አሸናፊው ክለብ ወልቂጤ ከተማ ነጥቡን 12 በማድረስ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ 2ኛ ላይ ተቀምጧል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ነገሌ አርሲ ወደ ሊጉ መሪ ተጠግቷል

በሳምንቱ የማሳረጊያ ቀን በተደረገ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ወደ ሊጉ መሪ የቀረበበትን ድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...