By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ቡናማዎቹ አፄዎቹን ሲረቱ ሐይቆቹ በመጥፎ ጉዟቸው ቀጥለዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎችሀዋሳ ከተማኢትዮጵያ መድህንፋሲል ከነማ

ቡናማዎቹ አፄዎቹን ሲረቱ ሐይቆቹ በመጥፎ ጉዟቸው ቀጥለዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 14ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም በዛሬው ዕለት ተደርገዋል።

በዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡናን ከፋሲል ከነማ አገንኛቶ በቡናማዎቹ የ1 – 0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

ለአሰልጣኝ ነፃነት ክብሬው ቡድን የማሸነፊያውን ግብ ዲቫይን ዋችኩዋ በ66ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

አንተነህ ተፈራ ከበፍቃዱ አለማየሁ የተቀበለውን ኳስ በሳጥኑ የግራ አቅጣጫ ይዞ ገብቶ ወደ ግብ ሞክሮት በግብ ጠባቂው ዮሐንስ ደርሶ ቢመለስም በቅርብ የነበረው ዲቫይን ዋቹኩዋ ከመረብ አሳርፎታል።

- ማሰታውቂያ -

ግቡም ለናይጄሪያዊው ተጫዋች በቡናማዎቹ ማልያ ያስቆጠረው ሁለተኛ ግቡ ሆኖ ተመዝግቧል።

ውጤቱንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና ነጥቡን 17 በማድረስ ወደ 7ኛ ከፍ ማለት ችሏል።

ጨዋታውን ግብ ሳይቆጠርባቸው ያጠናቀቁት ቡናማዎቹ ባለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ምንም ግብ ሳያስተናግዱ መቀጠል ችለዋል። ይህም በውድድር ዘመኑ በአምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ባለማስናገድ ብቸኛ ቡድን አድርጓቸዋል።

በተጨማሪም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም ተከታታይ ያለመሸነፍ ጉዟቸውን 10ኛ ጨዋታ ላይ አድርሰዋል።

በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው ፋሲል ከነማ በበኩሉ ሌላ መጥፎ ሽንፈትን ያስተናገደበት ዕለት ሆኖ አልፏል።

ኢትዮጵያ ቡናን በ2003 ዓ.ም የሊግ ዋንጫ አሸናፊ ማድረግ የቻሉት ውበቱ አባተ ፋሲልን እየመሩም ለመጀመሪያ ጊዜ በቀድሞ ክለባቸው ተረተዋል።

በውድድር ዘመኑ በሶስት ጨዋታዎች ብቻ ድል የቀናው የጎንደር ከተማው ተወካይ ከአምስት ሽንፈት አልባ ጨዋታዎች በኋላ ሽንፈትን ቀምሷል።

ቡድኑ በቀጣይ ከሚያደርጋቸው ተከታታይ አራት ጨዋታዎች መካከል በሶስቱ በደረጃ ሰንጠረዡ እስከ አራተኛ(መቻል ፣ ኢትዮጵያ መድኅን እና ባህር ዳር ከተማ) ከሚገኙ ክለቦች ጋር ማድረጉ ደግሞ ሁኔታዎችን ሊያከብድበት እንደሚችል እንዲገመት አድርጓል።

አፄዎቹ አሁን ላይ ከወራጅ ቀጠናው በሁለት ነጥቦች ብቻ ርቀት ላይም ይገኛሉ።

በ15ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ፋሲል ከነማ የሊጉን መሪ መቻልን ሲገጥም ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ በሳምንቱ አራፊ ቡድን ነው።

በዕለቱ ሁለተኛ እና በሳምንቱ የመጨረሻ መርሐግብር ኢትዮጵያ መድኅን ሀዋሳ ከተማን 2 – 0 ረቷል።

በጨዋታው መሐመድ አበራ እና ዳዊት ተፈራ የኢትዮጵያ መድኅንን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።

በአሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ የሚመራው መድኅን በተከታታይ እያስመዘገባቸው ባለው ውጤቶች ከመሪው መቻል በሁለት ነጥቦች ርቀት ብቻ ለመቀመጥ ችሏል።

ቡድኑ የውድድር ዓመቱ ብቸኛውን ሽንፈት በሶስተኛው ሳምንት በሲዳማ ቡና ካስተናገደ በኋላ ባለፉት ተከታታይ ዘጠኝ ጨዋታዎች አልያም 88 ቀናት ያለ ሽንፈት መጓዝ ችሏል። ቡድኑ በዚህ ጉዞው በስድስቱ ጨዋታዎች ሶስት ነጥቦችን ይዞ ወጥቷል።

በተጨማሪም በመከላከል ረገድ ጠንካራ ሆኖ የቀጠለው ቡድኑ ከ12 ጨዋታዎች ለሰባተኛ ጊዜ ግብ ሳያስተናግድ ያጠናቀቀበት ጨዋታ ሆኗል።

እጅግ መጥፎ የውድድር ዘመን እያሳለፈ ያለው ሀዋሳ ከተማ በበኩሉ በሊጉ ከድል ከተራራቀ ሶስተኛ ወሩን ደፍኗል።

ክለቡ አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉን አሰናብቶ በጊዜያዊ አሰልጣኞች ቢመራም በኢትዮጵያ ዋንጫ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከረታበት ጨዋታ ውጪ በሊጉ ደጋፊዎቹን ማስደሰት አልቻለም።

ባሳለፍነው የውድድር ዘመን በተለይም በኤርትራዊው አሊ ሱሌይማን የሚመራው የፊት መስመሩ በርካታ ግቦችን ማስቆጠር ቢችልም ዘንድሮ እስካሁን ባለው ቁጥር የሊጉ ሁለተኛ ዝቅተኛ ግብ አስቆጣሪ ቡድን ሆኗል።

ባለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎችም ሐይቆቹ ኳስና መረብን አንድም ጊዜ ማገናኘት አልቻሉም።

ቡድኑ አሁንም ከ13 ጨዋታዎች 10 ነጥቦችን ብቻ በመያዝ ወልዋሎ አዲግራትን ብቻ በልጦ 17ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

በቀጣይ ሳምንት ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ ከተከታዩ ወልዋሎ አዲግራት ሲገናኝ ኢትዮጵያ መድኅንም ተከታዩን ባህርዳር ከተማ ይገጥማል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የሊጉ መሪ ነጥብ ሲጥል የዓምናው ሻምፒዮን ወደ ድል ተመልሷል
Next Article አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነ ማሪያም ፣ ዮናስ ለገስ ፣ አማኑኤል ኤርቦ ፣ ሄኖክ ተወልደ እና አሮን አንተር የጨዋታ እገዳ ተጣለባቸው

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችLIVESCORE

ጅማ አባጅፋር ከ አዳማ ከተማ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ

hatricksport team By hatricksport team 5 years ago
የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ዕጣ ማውጣት መርሐ ግብር ተከናወነ
አፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ | ጅማ አባጅፋር ከ አል’አህሊ በቀጥታ ውጤት /LIVESCORE/ ይከታተሉ
ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቫዝ ፒንቶ ተለያዩ።
ኢትዮ ኤሌክትሪክ አማካይ አስፈረመ !!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?