By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ነገሌ አርሲ 19 ነጥብ ላይ የደረሰበትን ድል ሲያስመዘግብ አዳማ ከተማ የውድድር ዘመኑን 5ኛ ድል አሳክቷል
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችድሬዳዋ ከተማአዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባነጌሌ አርሲሽረ ምድረገነት

ነገሌ አርሲ 19 ነጥብ ላይ የደረሰበትን ድል ሲያስመዘግብ አዳማ ከተማ የውድድር ዘመኑን 5ኛ ድል አሳክቷል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 2 months ago
Share
SHARE

ነገሌ አርሲ እና አዳማ ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል

በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት የሁለተኛ ዕለት የአዲስ አበባ ስታድየም ጨዋታዎች ነገሌ አርሲ እና አዳማ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል።

በቀዳሚነት ከ07:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ ነገሌ አርሲ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 0 አሸንፏል።

በሁለቱም በኩል ተመጣጣኝ የሚባል እንቅስቃሴ በታየበት የጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ከመስመር በሚነሱ ኳሶች ዕድሎችን ፈጥረዋል።

- ማሰታውቂያ -

በጨዋታውም የመጀመሪያው ግብ የተገኘው በአስረኛው ደቂቃ ላይ በነገሌ አርሲ በኩል ነበር።

አስደናቂ የውድድር ዘመን እያሳለፈ የሚገኘው ከቤ ብዙነህ ከሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ የቀነሰለትን ኳስ ሐቢብ ከማል ግብ አድርጎታል።

ከግቡ በኋላ ድሬዳዋ ከተማዎች ከራሳቸው የሜዳ ክፍል በመነሳት ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በመድረስ ዕድሎችን ለመፍጠር ቢጥሩም የነገሌ አርሲው የግብ ዘብ እድሪሱ አብዱላሂን የፈተኑ አልነበሩም።

የሚነጥቋቸውን ኳሶች በፈጣን ሽግግር ወደ ድሬዳዋ ከተማ ሳጥን የሚያደርሱት ነገሌ አርሲዎች በ26ኛው እና በ33ኛው ደቂቃዎች ላይ በከቤ ብዙነህ አማካይነት ጠንካራ የግብ ሙከራዎችን አድርገው የነበረ ቢሆንም አብይ ካሳዬ ግብ ከመሆን አድኗቸዋል።

በቀጣዮቹ የመጀመሪያ አጋማሽ ደቂቃዎች ላይ መሐመድኑር ናስር እና አቤል ነጋሽ ጥሩ አጋጣሚዎችን መፍጠር ቢችሉም ኳሱን ከመረብ ውስጥ መቀላቀል አልቻሉም።

በሁለተኛው አጋማሽ የድሬዳዋ ከተማ ጫና ተጠናክሮ ሲቀጥል ነገሌ አርሲዎች በጥብቅ መከላከል ግባቸውን ሲጠብቁ በፈጣን እና ረጃጅም ኳሶች ደግሞ ዕድሎች ፈጥረዋል።

አጋማሹ በጀመረ በሰከንዶች ውስጥ አቤል ነጋሽ በግቡ ትይዩ በቅርብ ርቀት ያገኘውን ኳስ ከግቡ አግዳሚ በላይ ልኮታል።

በ64ኛው ደቂቃ ላይም አቤል ነጋሽ በተመሳሳይ ከሳጥን ውስጥ ግብ የማስቆጠር ዕድልን ቢያገኝም እድሪሱ አብዱላሂ አድኖበታል።

በረጃጅም ኳሶች የድሬዳዋ ከተማ ተከላካዮች ጀርባ ላይ ያለውን ቦታ ለመጠቀም ሲጥሩ የቆዩት ነገሌ አርሲዎች በ78ኛው ደቂቃ ላይ የናትናኤል ሰለሞን ድንቅ አጨራረስ በታየበት ግብ መሪነተቻውን ወደ 2 ለ 0 ከፍ አድርገዋል።

የጨዋታው መጠናቀቂያ የፊሽካ ድምፅ በሚጠበቅበት ጊዜም የድሬዳዋ ከተማ ተከላካዮች ስህተትን ተጠቅሞ አለኝታ ማርቆስ የነገሌ አርሲን 3ኛ ግብ አስቆጥሮ ነገሌ አርሲን የ3 ለ 0 አሸናፊ አድርጓል።

ውጤቱንም ተከትሎ ቡድኑ ነጥቡን 19 ማድረስ ሲችል ድሬዳዋ ከተማ በነበረው 16 ነጥብ ለመቆየት ተገዷል።

በ13ኛው ሳምንት ነገሌ አርሲ ከመቻል እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማ ከባህርዳር ከተማ ይጫወታሉ።

ከ10:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ ደግሞ አዳማ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን 1 ለ 0 ረቷል።

በሁለቱም በኩል ቀድሞ የጨዋታውን ግብ ለማስቆጠር ጥረቶች በታዩበት ጨዋታው በተለይም የመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ ግቦች የሚስተናገዱበት ይመስል ነበር።

በጨዋታ እንቅስቃሴ አዳማ ከተማዎች በአንፃራዊነት የተሻሉ ዕድሎች መፍጠር የቻሉ ሲሆን በምድረ ገነት ሽረ በኩል በተደጋጋሚ ከጨዋታ ውጪ በመሆን የማጥቃት ሂደታቸው ይቋረጥ ነበር።

የጨዋታው የመጀመሪያ ኢላማውን የጠበቀ የግብ ሙከራ በ12ኛው ደቂቃ ላይ የተደረገ ሲሆን ሳዲቅ ኑሩ ከቅጣት ምት በቀጥታ ወደ ግብ የሞከረው ኳስ ሪችሞንድ አይ መልሶታል።

በአዳማ ከተማ በኩል አህመድ ሁሴን ከነቢል ኑሪ የደረሰውን ድንቅ ኳስ ከግብ ጠባቂው ጋር ተገናኝቶ ያመከነበት እና የአቡበከር ሳኒ መነሻውን ከማዕዘን ምት ያደረገ ኳስ ወደ ግብ ሞክሮ በሪችሞንድ አይ የተመለሰበት ኳሶች ተጠቃሽ ናቸው።

በምድረ ገነት ሽረ በኩል በአጋማሹ የመጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ በሽመክት ጉግሳ አማካይነት ያደረጉት ሙከራ እና ዳንኤል ዳርጌ በረጅም የተላከለትን ኳስ አላዛር ማርቆስ ከግቡ ወጥቶ እንዳይጠቀም ያደረገበት አጋጣሚዎች ተጠቃሽ ናቸው።

በሁለተኛው አጋማሽ በድጋሚ በፈጣን እንቅስቃሴ ጨዋታው ሲቀጥል ጠንካራ የግብ ሙከራዎችን ለመመልከት ግን ደቂቃዎች መጠበቅ የግድ ብሎ ነበር።

በ56ኛው ደቂቃ ላይ ቢንያም አይተን ከአብድልከሪም መሐመድ የደረሰውን ኳስ ለአህመድ ሀሱን በጥሩ መልኮ ቀንሶለት የነበረ ቢሆንም ጠንካራ ያልሆነው የአህመድ የግብ ሙከራ በሪችሞንድ አይ በቀላሉ ተይዟል።

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ የዳንኤል ዳርጌ ብልጠት በታየበት የማጥቃት ሂደት ራሱ ዳንኤል ዳርጌ ኳሱን መልሶ አግኝቶ ያደረገው ጠንካራ ሙከራ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል።

ጠንካራ ካሉ የግብ ሙከራዎች የተራራቀው ጨዋታው 85ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ ግብ አስተናግዷል።

የአዳማ ከተማ ቁልፍ ተጫዋች የሆነው ቢንያም አይተን በተጠቀሰው ደቂቃ ላይ ከቡድን አጋሩ የደረሰውን ኳስ ገፍቶ ወደ ሳጥን በመግባት ቡድኑም አሸናፊ ያደረገ ግብ አስቆጥሯል።

በውድድር ዓመቱ 5ኛ ድሉን ያሳካው አዳማ ከተማ የዛሬ ድሉን ተከትሎ ነጥቡን 20 ያደረሰ ሲሆን ምድረ ገነት ሽረ በነበረው 14 ነጥቦች ላይ ለመቆየት ተገዷል።

በ13ኛው ሳምንት አዳማ ከተማ ከፋሲል ከነማ ምድረ ገነት ሽረ ደግሞ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ጨዋታዎቻቸውን ያደርጋሉ።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ሲዳማ ቡና ወደ ሊጉ መሪነት ሲመለስ ሀድያ ሆሳዕናንም አሸንፏል
Next Article ቡናማዎቹ ጦሩን ሲረቱ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዓመቱ ለሶስተኛ ጊዜ አሸንፏል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንዜናዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሞሮኮ 4-0 ተሸንፈ

Mussie Girmay By Mussie Girmay 8 years ago
ወልቂጤ ከተማ ከ አዳማ ከተማ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
”በ2014 የዉድድር አመት የተሻለውን ታፈሰ ሰርካ ጠብቁ”
” የሊጉ ጨዋታዎች አሁን ባለው የቫይረሱ ስርጭት ሊቋረጥ ይችላል ” መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ
የፕርሚየር ሊግ ሼር ካምፓኒ ህጋዊ ፍቃድ አገኘ !
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?