መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጅማ ስታዲየም ዝግጅትን በተመለከተ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጅማ ስታዲየም ዝግጅትን በተመለከተ

አጋራ
አጋራ

 

ግዙፉ የጅማ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን ለማስተናገድ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።

የመጀመሪያ ዙር የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከሚያስተናግዱት ስታዲየሞች መካከል አንዱ የሆነው የጅማ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም ሲሆን የሀገሪቱን ትልቅ ውድድር የሆነው የ ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን ከ ሰባተኛው እስከ አስራ አንደኛው ሳምንት ያሉ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት ዕድሉን አግኝቷል።

ተሳታፊ የሆኑት የሊጉ ክለቦች ከ ቅዳሜ ጀምሮ ወደ ጅማ መግባት የጀመሩ ሲሆን አሁን ላይ ሁሉም ክለቦች ካምፓቸውን አዘጋጅተው የጅማ ከተማ ዋናው ሜዳን ጨምሮ በሌሎች በተለያዪ በተዘጋጀላቸው የመለማመጃ ሜዳ ልምምዳቸውን እያደረጉ ይገኛሉ።

ጨዋታውን በቀጥታ ቴሌቪዥን የሚያሰራጨው የሱፐር ስፖርት የቡድን አባላትም ጅማ ከተማ የገቡ ሲሆን የመጫወቻ ሜዳውም ሙሉ ለሙሉ ለጨዋታ ዝግጁ እንደሆነ ሀትሪክ ስፖርት ድህረገጽም በስፍራው ተገኝታ ለማረጋገጥ ችላለች ።

ሆኖም ጨዋታውን በቀጥታ የሚያስተላልፈው የ ዲ ኤስ ቲቪ የቴሌቪዥን ተንቀሳቃሽ መኪናም ከጉምሩክ ጋር በተያያዘ ችግር ዘግይቶ ዛሬ ከሰዓት ከአዲስአበባ ወደ ጀማ ያመራ ሲሆን ማምሻውን ቦታው ላይ በመገኘት ለነገው ጨዋታ ዝግጅታቸውን እንደሚያጠናቅቁ ይጠበቃል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...