By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “በጥሩ አቋም ለቀጣዮቹ አስር አመታት የመጫወት ብቃት አለኝ” ምንተስኖት አዳነ/ቅዱስ ጊዮርጊስ/
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

“በጥሩ አቋም ለቀጣዮቹ አስር አመታት የመጫወት ብቃት አለኝ” ምንተስኖት አዳነ/ቅዱስ ጊዮርጊስ/

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 5 years ago
Share
SHARE

ከእኛና ከጠራናቸው እንግዶች በላይ እግዚአብሄር እንዲከብር ነበር የፈለግነው ደግሞም ተሳክቶልናል….”

“በጥሩ አቋም ለቀጣዮቹ አስር አመታት የመጫወት ብቃት አለኝ”
ምንተስኖት አዳነ/ቅዱስ ጊዮርጊስ/

ፈረሰኞቹ ባሳለፍናቸው ጥቂት ቀናቶች ስማቸው ከእግርኳስ ውጪ በሆነ ነገር ሲጠራ ሰምተናል….የቡድኑ ተጨዋቾች የሆኑት ምንተስኖት አዳነ ከወ/ሮ ኢትዮዽያ አቤል ያለውም ከወ/ሮ ጋር ባለፈው እሁድ ጋብቻቸውን መፈጸማቸው ትኩረት የሳበ ሆኗል…ተጨዋቾቹ ሃላፊነት መሸከም እንደሚችሉና ሃላፊነት መሸከም እንደማይፈሩም ያሳዩበት ተደርጎ ተወስዷል።

የሃትሪክ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ሁለቱንም ተጨዋቾች ቃለ ምልልስ ለመስራት ፈልጎ ወደ ሁለቱ ተጨዋቾች የግል ስልክ ይደውላል በተደጋጋሚ ጊዜ ቢደወልም መልእክት ቢላክም አቤል ያለው ምላሽ ሳይሰጥ በመቅረቱ ልናገኘው አልቻልንም ነገር ግን ምንተስኖት አዳነ በወቅቱ ቤተሰባዊ ፕሮግራም ቢኖረውም ጊዜውን አጣቦ ከሀትሪኩ ዮሴፍ ከፈለኝ ጋር ያደረገው አጠር ያለ ቆይታ የሚከተለውን ይመስላል። በዚህ አጋጣሚ የዝግጅት ክፍሉ ለሁለቱም ተጨዋቾች መልካም ጋብቻ እንዲሆንላቸው ይመኛል።

- ማሰታውቂያ -

ሀትሪክ:- ሀገራችን ኢትዮዽያ እንዴት ናት?

ምንተስኖት:- /ሳቅ በሳቅ/ ሀገሬና ባለቤቴን የሚመለከት ጥምር ጥያቄ ነው/ሳቅ/ በጣም ደህና ናቸው….የኔ ኢትዮዽያም ደህና ናት

ሀትሪክ:- ኢትዮዽያ ለሚለው ስም ያለህ ስሜትስ ምን ይመስላል?

ምንተስኖት:- ስሙ የሚወደድ ስም ነው። እንደ ሀገርም ኢትዮዽያን እወዳለሁ ሀገሩን የማይወድ ሰው የለም የምወዳት የባለቤቴና የሀገሬ ስም መመሳሰሉ ደግሞ ትልቅ ደስታ ይፈጥራል

ሀትሪክ:- ትዳር መስርተሃል..እንዴት አገኘኽው?

ምንተስኖት:- ትዳር ከመሰረትኩ ገና አራት ቀኑ ነው/ቃለ ምልልሱን የሰራነው ሀሙስ እለት ነው/ በአራቱ ቀን ባየሁት አሪፍ ነው አሁንም ገና ከሰርጉ ቀን ስሜት አልተላቀቅንም በራሳችን ጊዜ ላይም አይደለንም አሁንም ከበባ አለው…/ሳቅ/

ሀትሪክ:- ባለትዳር የሚለውን ከጋብቻ በፊትና በኋላ ያለውን ትርጉም እንዴት ትገልጸዋለህ?

ምንተስኖት:- ትልቅ ልዩነት አለው ከጋብቻ በፊት ሁሉ ነገር ራስ ተኮር ብቻ ነበር አሁን ካገባሁ በኋላ ግን ለብቻዬ አልችልም ከሰው ጋር የመኖር ጉዳይ ይሆናል.. ባለቤትህን ታሳቢ አድርገህ ነው የምትጓዘው ፕሮግራምህ የግል አይሆንም በጊዜ መግባት ካለብህ ትገባለህ ወጣ ማለት ብፈልግ ከባለቤቴ ጋር ተነጋግሬ ነው እናም ባለ ትዳር ሲኮን ለብቻህ አይደለም አብረህ የምትኖርለት ሰው አለ..ያ ለውጥ ግን ያስደስታል.

ሀትሪክ:- የሰርግህ እለት ምን ተሰማህ? እንዴትስ አለፈ?

ምንተስኖት:- አሪፍ ጊዜ ነበር ትንሽ ሰው ነው የተጠራው.. ቤተሰቦቻችንና የቅርብ የምንላቸውን እንግዶች ብቻ ነበር የጠራነው… ፕሮግራሙ መንፈሳዊ ይዘቱን ሳይለቅ እንዲሄድ ነበር የፈለግነው… በዚህ መንገድ እንዲካሄድ ስንወስን ፈተና ነበረው..ሰርግ ተሰርጎ መጠጥ እንዴት አይኖርም በሚል ቅሬታ ተነስቶ ነበር…ሁለታችንም ግን ጠንካራ አቋም በመያዛችን፣ እግዚአብሄር እንዲከብር በመፈለጋችን፣ የምንከተለው እምነት አስተምሮ ይህን ስለሚደግፍ የምንፈልገውን አድርገናል እግዜር ይመስገን ከፕሮግራሙ በኋላ የነበረው ሰዉ ሁሉ መደሰቱን ብዙ ነገር መማሩን ገልጾልናል…በዚህም ደስ ብሎናል..ከእኛና ከጠራናቸው እንግዶች በላይ እግዚአብሄር እንዲከብር ነበር የፈለግነው ደግሞም ተሳክቶልናል….

ሀትሪክ:- በሰርጉ እለት የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ ፕሬዚዳንት አቶ አብነት ገ/ መስቀል ተገኝተዋል የከለቡ አመራሮችና ተጨዋቾቹ ስለ ስነምግባርህ ምስክርነት ሲሰጡህ ምን ተሰማህ?

ምንተስኖት:- በጣም ደስ ብሎኛል…ያው እንደሚታወቀው ስላንተ ከቤተሰብ በላይ ማንም ምስክርነት መስጠት አይችልም…. ለ13 አመታት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ግልጋሎት ሰጥቻለሁ.. ቅዱስ ጊዮርጊስም ታዳጊ ሆኜ ወጣት የሆንኩበት ወደ ጎልማሳነትም የተጓዝኩበት ክለብ ነው ሌላኛው ቤተሰቤ ነው ማለት እችላለሁ የሚያውቁትን በመመስከራቸው ደስ ብሎኛል..ሁሉንም አመሰግናለሁ..

ሀትሪክ:- ትዳር መያዝህ ሀላፊነት ጨምሮብሃል?

ምንተስኖት:- /ሳቅ/ አዎ ምንም ጥያቄ የለውም ትዳር ሃላፊነት ይጨምራል..እኔ ግን ከትዳር መያዜ በፊት ነው ሃላፊነቱን እየተወጣሁ ያለሁት/ሳቅ/ በተለይ ትዳር ላይ መኖር የለባቸውም የሚባሉት ደባል ነገሮች ስለሌሉብኝ ቀለል ባለ መልኩ ሀላፊነቴን እየተወጣሁ ነው… አስቀድሜም ግን የቤተሰብ ሰው ስለሆንኩ ሀላፊነቱ አልከበደኝም

ሀትሪክ:- ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያለህ ግንኙነት ምን ይመስላል?

ምንተስኖት:- አሁን በሰርጌ ደስታ ውስጥ ነኝ ስለዚህ አይነቱ ጉዳይ ማሰብ አልጀመርኩም ምናልባት ከሰኞ በኋላ ነው ስለጉዳዩ መንቀሳቀስ የምፈልገው.. ቀጣዮቹ ቀናቶች የሚያሳውቁን ነገር ይኖራል…

ሀትሪክ:- አሁን ቅዱስ ጊዮርጊስና ምንተስኖት ተለያይተዋል ማለት ይቻላል?

ምንተስኖት:- አሁን ላይ ምንም ማለት አልችልም..እቀጥላለሁ አልቀጥልም የማውቀው ነገር የለም ቀጣዮቹ ቀናቶች የሚያመጧቸው ነገሮች ይኖራሉ ብዙ የጨዋታ አመታቶች እንዳሉኝ ግን ተስፋ አደርጋለሁ ከውሳኔ በፊት ግን ከባለቤቴና ከቤተሰቤ ጋር ቁጭ ብዬ መምከር አለብኝ

ሀትሪክ:- ስንት የተጨዋችነት አመታቶች ይኖሩኛል ብለህ ታምናለህ?

ምንተስኖት:- ቀድሞ የመታወቁ ነገር ካላስረጀኝ በስተቀር በጥሩ አቋም ለቀጣዮቹ አስር አመታት የመጫወት ብቃት አለኝ ። አንድ የማውቀው ታሪክ ልንገርህ.. ልጁ ብዙ ባይታወቅም ልጅ ሆነን ስናድግ እያጨበጨብንለት ኳስ ሲጫወት የምናውቀው ልጅ በስመ ወጣት ነው አሁን እየተጫወተ ያለው..ይሄ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር አሁን ወደ ሃያዎቹ መጨረሻ ላይ ነው የምገኘው ይሄ እድሜ ደግሞ በብቃት ለመጫወት የሚያስችል ነው..

ሀትሪክ:- በቀጣይ የት ልናገኝህ እንችላለን?

ምንተስኖት:- የመጫወት አቅም እንዳለኝ ብቻ ነው የማውቀው… በቅርብ ጊዜ ውስጥ ግን ሁሉም ነገር ሊታወቅ እንደሚችል እንጂ አሁን መልስ የለኝም/ሳቅ/

ሀትሪክ:- ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች የምትለው ነገር አለ?

ምንተስኖት:- ትልቅ ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ ከወጣትነቴ ጀምሮ ለነበራቸው ድጋፍ ከልብ አመሰግናለሁ በዚሁ አጋጣሚ ከጊዮርጊስ ውጪ ያሉ የሌላ ክለብ ደጋፊዎችም መንገድ ላይ ሲያገኙኝ የሚሰጡኝ አክብሮትና አድናቆት አስደስቶኛል እነሱንም አመሰግናለሁ

ሀትሪክ:- የመጨረሻ ምስጋና ካለህ…?

ምንተስኖት:- የነገሮቼ ጀማሪና ፈጻሚ የሆነውን ልዑል እግዚአብሄርን ከልብ አመሰግናለሁ…መላው ቤተሰቦቼን፣ ውዷ ባለቤቴን፣ ሚዜዎቼን ያገዙኝን ጓደኞቼንም ከልብ አመሰግናለሁ.. ወንድሜ ዮናስ አዳነንም ከልብ አመሰግናለሁ ሁሉ ነገሮች መስመር እንዲይዝ በተለይ የዚህ አይነት የማስተባበር ነገሮችን ቦታ ቦታቸውን እንዲይዙ የማድረግ አቅም የለኝም ሰርግ ቦታ እንኳን ብዙ ጊዜ የምሄድ አይነት ሰው አይደለሁምና ይህን ክፍተት ተረድቶ ሁሉ ነገር ላይ ገብቶ ሀላፊነቱን በሚገባ ተወጥቷልና ከልብ አመሰግናለሁ…

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article ሰበታ ከተማ አምስት ተጫዋቾችን አስፈርሟል!!
Next Article የኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የምድብ ለ ሁለተኛ ዙር ጨዋታ ወንዶ ገነት አሊ ሀብቴ ጋራዥን የጋምቤላው ኑዌር ዞን አሳይታ ወረዳን ከፍፁም የጨዋታ ብልጫ ጋር አሸንፈዋል።

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንዜናዎች

ዜና | የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ1ኛ ዙር ግምገማ ዛሬ ተካሄደ።

Mussie Girmay By Mussie Girmay 8 years ago
ለአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን አመራርነት ሰራዊት ፍቅሬ ታስቦ ማስተዋል ወንድወሰን ተመረጠች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ እና ከፍተኛ ሊግ የዕጣ ማዉጣት ስነስርዓት ተካሂዷል !!
ፈረሰኞቹ እንግሊዛዊ አሰልጣኝ ቀጠሩ
“ውጤት ካጣንባቸው ካለፉት ግጥሚያዎች ተምረናል፤ ወደላይም ልንነሳ ተዘጋጅተናል”የአብስራ ተስፋዬ /ቅ/ጊዮርጊስ/
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?