By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “ኢት.ቡናን የለቀኩት በቤተሰብ ችግር እንጂ በገንዘብ አይደለም ወደ ቤቴም በመመለሴ ደስ ብሎኛል” በረከት አማረ/ኢት.ቡና/
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡና

“ኢት.ቡናን የለቀኩት በቤተሰብ ችግር እንጂ በገንዘብ አይደለም ወደ ቤቴም በመመለሴ ደስ ብሎኛል” በረከት አማረ/ኢት.ቡና/

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 5 years ago
Share
SHARE

ሀትሪክ:- እንኳን ወደ ቤትህ ተመለስክ ነው የሚባለው..?

በረከት:- /ሳቅ/ የምወደውን ክለብ በመቀላቀሌ በጣም ደስ ብሎኛል አምና የሄድኩት አባቴ በማረፉ ሀዘን ሆኖ የግድ የቤተሰብ ነገር ሆኖብኝ እንጂ ኢትዮዽያ ቡናን መልቀቅ አልፈለኩም ነበር..ዳግም ይህን እድል ስላገኘሁ ግን ተደስቻለሁ

ሀትሪክ:- ዝውውሩ ፈጠነ..ምናለባት በሁለታችሁም መሃል መፈላለጉ ስለነበር ይሆን?

በረከት:- በሁለታችንም መሃል ፍላጎቱ ስለነበር ነው የቀለለው በደንብ ነው የተፈላለግነው..በዚህም ደስ ብሎኛል

- ማሰታውቂያ -

ሀትሪክ:- የተክለ ማርያም ሻንቆ/ጎሜዝ/ ተተኪ መሆን ሃላፊነቱን ከበድ አያደርገውም?

በረከት:- ደጋፊው ከሚፈልገው አንጻር የውጪው ጨዋታ ታክሎበት ጫና ሊኖረው ይችላል እንደምንም ጫናውን እንደምቋቋመው ግን ርግጠኛ ነኝ አምናም ክለቡ ውስጥ በመኖሬ እቸገራለሁ ብዬ አልሰጋም

ሀትሪክ:- በጅማ አባጅፋር የነበረህ ቆይታ ምን ይመስላል?

በረከት:- ከእረፍት ስለመጣሁ አሪፍ ነበር ቡድኑን ደግሞ ጠቅመነው ከመውረድ ተርፏል ያደረግነው ቆይታ ከደመወዝ ጋር እየተንገጫገጨ ቢሆንም በፕሪሚየር ሊጉ መቆየቱ አስደስቶኛል። በርግጥ ደመወዝ ላይ ያለው ሁኔታ ቅር ያሰኛል ሁሉ ተስተካክሎ ኳሱ ላይ ብቻ ማሰብ የግድ ነው እዚያ ግን ደመወዙ ጥቅማ ጥቅሙ ሲቀር ቅር ያሰኛል። ዋናው ማለፉ ቢሆንም ለቀጣዩ መሰራት እንዳለበት ያሳያል። ጅማ አባጅፋር ሲባል 2010 ላይ ዋንጫ የወሰደ ትልቅ ቡድን እንደመሆኑ ችግሮቹ ተወግደው የተሻለ ጊዜ እንዲመጣ እመኛለሁ…

ሀትሪክ:- ከአቤል ማሞ ጋር ለሚኖረው የቋሚ ተሰላፊነት ፍልሚያ ዝግጁ ነህ?

በረከት:- /ሳቅ/ ያው እግር ኳስ ላይ ያለ ነገር ነው..ጥሩ ሆኜ ለመገኘትና ለመሰለፍ እጥራለሁ ፉክክሩ ራሱ ለቡድኑ ትልቅ ጥቅም ይኖራል ብዬ አስባለሁ በሁለታችን መሃል ጤናማ ፉክክር እንደሚኖር ተስፋ አደርጋለሁ
ሀትሪክ:- ብዙ ጊዜ ለተሰላፊነት ያለው ፉክክር ጤናማ አይደለም ይባላል..እናንተ ጋርስ ይሄ ሊከሰት ይችላል?

በረከት:- /ሳቅ/ ተጠባባቂ ግብ ጠባቂ ቋሚ ተሰላፊ የመሆን እድሉ ጠባብ ነው..በቀይ ካርድ ወይም ጉዳት ካልሆነ በስተቀር ቋሚው የመቀየር እድሉ አናሳ ነው…ያም ሆኖ ኳስን በኳስ ባህሪ መያዝ ይኖርብናል ለክለቡ ድል የግብ ጠባቂው ጥሩ መሆንን ካልተመኘህ ተቀይሮ የገባው ላይሳካለት ይችላልና ተሳስቦ መኖር ይቀላል ባይ ነኝ እኔ ጋር ያለው ልብ አሪፍ ነው

ሀትሪክ:- የሀገር ውስጥ ግብ ጠባቂዎች ይመቹሃል?

በረከት:- ሁሉም ምርጥ ናቸው በግሌ ግብ ጠባቂ የሆንኩት አዲግራት ላይ እያየሁ ያደኩት የማነ የሚባል ግብ ጠባቂ ፈለግ ተከትዬ ነው የጀመርኩትና ሁሉም ለኔ አሪፍ ናቸው እነ አቤል ጎሜዝና እነ ጀማል ጥሩ የሚባሉ ናቸው በረኞቻችን ጎበዝ መሆናቸውን አውቃለሁ..

ሀትሪክ:- የውጪ በረኛ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አልተከለከለም..በብሄራዊ ቡድን ላይ ተጽእኖ አይፈጥርም?

በረከት:- ተጽእኖውማ አይቀርም በደንብ ነው የሚፈጥረው ትልቁ ችግር ደግሞ በአቋምህ ብትበልጥም ቋሚ ሆኖ መሰለፉ ራሱ አጠራጣሪ ነው በልጠህም ቢሆን በብዙ ገንዘብ ስለሚገዟቸው እነሱን ቤንች ማድረግ ይከብዳቸዋል..ያ ደግሞ ሀገር ይጎዳል።ፌዴሬሽኑ ቢያየው ደስ ይለኛል

ሀትሪክ:- ኢትዮዽያ ቡና የገባኸው ካሳዬን ስለምትወድ ወይስ የቡና ወዳጅ ስለሆንክ?

በረከት:- ሁለቱም ይመስለኛል…ወልዋሎ አዲግራት እያለሁም ኢትዮዽያ ቡናን እወደው ነበር… አጋነንከው አትበሉኝ እንጂ ከቡና ጋር እየተጫወትኩ መዝሙራቸው ይመስጠኝና ኳሱን ትቼ ስለ ክለቡ የማስብበት ጊዜ ነበር ..ለዚህ ክለብ ምነው በተጫወትኩ ያሰኛል..በካሳዬ ስር ለመሰልጠን ስስማማና እድሉን ሳገኝ በይበልጥ ክለቡን ልወደው ችያለሁ…በካሳዬ ስር መሰልጠን ያስደስታል… ለሀገር የሚጠቅም ትልቅ ሃሳብ የያዘ አሰልጣኝ ስር መሰልጠኔ የበለጠ ቡናን እንድወድ አድርጎኛል ሁለቱንም ወድጄ ነው የመጣሁት…በሀዘን ምክንያት ቡናን መልቀቄ አሁን ድረስ ያበሳጫኛል…ኢት.ቡናን የለቀኩት በቤተሰብ ችግር እንጂ በገንዘብ አይደለም ወደ ቤቴም በመመለሴ ደስ ብሎኛል

ሀትሪክ:- በአውሮፓ የአንተን ልብ የያዙ ግብ ጠባቂዎች እነማን ናቸው…?

በረከት:- ሁለት በረኞችን በጣም እወዳቸዋለሁ እነሱም የባርሴሎናው ቴርስቴገንና የማን.ሲቲው ኤደርሰን ናቸው በጣም አደንቃቸዋለሁ

ሀትሪክ:- ምናልባት በእግርም መጫወት ስለምትወድ ይሆን? /በካሳዬ እምነት ግብ ጠባቂምኮ ተጨዋች ነው ይላል/

በረከት:- እውነት ነው ሲጀመር ራሱ በረኛ የሆንኩበት ምክንያት ግራ ይገባኛል..ኳስ ስጀምር ፕሮጀክትም ስጫወት አጥቂ ነበርኩ በእግር መጫወት በጣም እወዳለሁ..በርግጥ ግብ ጠባቂ ከሆንኩ በኋላ የገባኝ ቡድኔ የሚያጠቃው በበረኛ ነው ትርፍ ተጫዋቹ እርሱ ነውና…በረኛ በእጅ ብቻ ነው ብሎ ለሚያስብ የአሰልጣኝ ካሳዬም እምነት ትክክል ነው መታሰብ ያለበት ማጥቃትም ከበረኛ ይጀመራል

ሀትሪክ:- ለኢትዮዽያ ቡና ደጋፊዎች የምትለው ነገር ካለ…?

በረከት:- እግዚአብሄር ይመስገን በጥሩ ሁኔታ ተቀብለውኛልና አመሰግናለሁ አንዳንዶች በፊት በብር.ጉዳይ እንደወጣው አድርገው አስበዋል.. በፍጹም ግን ቡናን በብር ትቼ አልወጣሁም ይህን እንዲያውቁልኝ እፈልጋለሁ…ሌላው ቡና ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ አሪፍ ነው ከእግዚአብሄር ጋር ለዋንጫ ለአንደኝነቱ የምንፋለምበት አመት እንደሚሆን አምናለሁ..ከአጨዋወቱ ጋር ተያይዞ አሪፍ ነገር የምናሳይም ይሆናል። ደጋፊው የሚደሰትበት አመት እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ…ስለ አቀባበላችሁም አመሰግናለሁ…

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ ዳግም ወደ ቤቱ ተመለሰ!
Next Article ባህርዳር ከተማ አራተኛ ተጫዋቹን አስፈርሟል!!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎች

በእዳማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች መካካል የእርቀ ሰላም ስነርዓት ተካሄደ

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 7 years ago
የኢትዮጵያ ከ 20 ዓመት በታች ቡድን አሰላለፍ !
“የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለፊፋ የመክሰስ ሃሳባችንን ትተነዋል” አቶ በረከት ደረጀ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኢንተርሚዲየሪዎች ማኅበር ም/ፕሬዚዳንት
የኢ.እ.ፌ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ከብራዚል ኤምባሲ አምባሳደር ጋር ተወያዩ
” ውጤቱን በጸጋ እቀበላለሁ ምክንያቱም ከግለሰብ ሀገር ይበልጣል’ አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢት.እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?