ኢንስትራክተር አብርሀም መብራቱን በዋና አሰልጣኝነት ከቀጠሩ በኋላ ወደ ዝዉዉር ገበያዉ የገቡት ባህርዳሮች ላለፉት ቀናት የተለያዩ ተጫዋቾችን ማስፈረማቸዉ ይታወሳል።
አሁን ደግሞ የአማካኝ ስፍራ ተጫዋቾች የሆነዉን አለልኝ አዘነ ከሀዋሳ ከተማ ማስፈረማቸዉ ተረጋግጧል።
ከአርባምንጭ ታዳጊ ቡድን የተገኘዉ አልልኝ ያለፋትን ሁለት አመታት በሀዋሳ ከተማ ቤት ዉስጥ በጥሩ ብቃት መጫወቱ ይታወሳል፤ አሁን ደግሞ ለቀጣዩ የዉድድር አመት በባህርዳር ከነማ ቤት ለመጫወት ፊርማዉን አኑሯል።


