ከሸገር ከተማ ጋር የተለያየው አድናን ረሻድ ሀዋሳ ከተማን ተቀላቀለ።
በጅማ አባጅፋር ከብዙሀኑ ጋር መተዋወቅ የቻለው የአማካይ እና የመስመር ተጫዋቹ አድናን ረሻድ ከአዳማ ከተማ ጋር ሦስት የውድድር ዘመናትን ካሳለፈ በኋላ በያዝነው አመት ለሸገር ከተማ ለሁለት አመት መፈረሙ ይታወሳል።
ከሳምንት በፊት ከሸገር ከተማ ጋር አንድ አመት ከስድስት ወራት ኮንትራት እየቀረው መለያየቱን የነገርኳችሁ ይህ ተጫዋች ኪቲካ ጀማን ያጣው ሀዋሳ ከተማን በይፋ መቀላቀል ችሏል።
አስተያየት ይስጡ