መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና የሀድያ ሆሳዕና የፋይናንስ ሃላፊ ቅዳሜ ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ
ሀዲያ ሆሳዕናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

የሀድያ ሆሳዕና የፋይናንስ ሃላፊ ቅዳሜ ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

አጋራ
አጋራ

ከደረቅ ቼክ ጋር ተያይዞ ከቀናት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ውስጥ የዋሉት የሀድያ ሆሳዕናው የፋይናንስ ሃላፊ ከተከሰሱበት 11 ክሶች በ10ሩ ክሶች የፊታችን ቅዳሜና ማክሰኞ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተባለ።

ሀላፊው ለ15 ተጨዋቾች የደረቅ ቼክ ሰጥተዋል በሚል በ11 ክስ ተከሰው ትላንት አዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው በአንዱ ተጨዋች የ120 ሺህ ብር ክስ በ4 ሺ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ቢወሰንም በ10ሩ ክስ ወደ ማረፊያ ቤት እንዲመለሱ መደረጉ ታውቋል። በተመሳሳይ ክስ የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ማዶሮ በፖሊስ እየተፈለጉ ሲሆን ስለሁኔታው ለማጣራት በግል ስልካቸው ላይ ቢደወልም ዝግ በመሆኑ ምላሽ ማግኘት አልተቻለም።

በእግር ኳሱ የፍትህ አካላት ተቀባይነት ያጣው የክለቡ አመራሮች ክስ በመደበኛ የፍትህ ስርአትም መሸነፉን የሚያሳይ ሲሆን አሁን በደረሰው አዲስ መረጃ መሰረት የአዲሱ የክለቡ አሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት ውል ማጸደቅ አለመቻላቸውና የስራ ባልደረባቸው መታሰሩን የተረዱት የክለቡ የቦርድ አባላት ሙሉ የሆነ ተግባራዊ ምላሽና ውሳኔ ለመስጠት ዛሬ ወይም ነገ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተነግሯል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...