መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ተጫዋቾችን ከወላይታ ዲቻ አስፈርሟል
ቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየዝውውር ዜናዎች

ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ተጫዋቾችን ከወላይታ ዲቻ አስፈርሟል

አጋራ
አጋራ

በዘንድሮው የዉድድር አመት እንደተጠበቁት መሆን ያልቻሉት ፈረሰኞቹ ለቀጣዩ የዉድድር አመት ተጠናክረው ለመቅረብ ይረዳቸው ዘንድ ተጫዋቾችን ወደ ቡድናቸው መቀላቀል ጀምረዋል።

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ ዘንድሮ ጎልተዉ መዉጣት ከቻሉት ተጫዋቾች መካከል የሚጠቀሱት ሁለቱ የወላይታ ዲቻ ተጫዋቾች ቸርነት ጉግሳ እና በረከት ወልዴ ቅዱስ ጊዮርጊስን በይፋ ተቀላቅለዋል።

ፈጣኑ የመስመር አጥቂ ቸርነት ጉግሳ ስሙ ከተለያዩ ክለቦች ጋር በዝዉዉር ሲያያዝ ቢቆይም በመጨረሻም ማረፊያ ቅ/ጊዮርጊስ መሆኑ ተረጋግጧል። የመስመር አጥቂዉ ለሁለት አመት በሚቆይ የውል ስምምነት ፊርማዉን አኑሯል።

ሌላኛው የወላይታ ዲቻ ተጫዋች የሆነዉ አማካኙ በረከት ወልዴ እንደ ክለብ አጋሩ ቸርነት ሁሉ በሁለት አመት የኮንትራት ስምምነት ቅዱስ ጊዮርጊስን መቀላቀል ችሏል።

ሁለቱን ወሳኝ ተጫዋቾች ማስፈረም የቻሉት ቅዱስ ጊዮርጊሶች ምንም እንኳን እስከ አሁን ድረስ ዋና አሰልጣኝ መሾም ባይችሉም፤ በሚቀጥሉት ጊዜያት ዉስጥ በዝዉዉሩ በንቃት በመሳተፍ ተጫዋቾችን ወደ ክለቡ እንደሚቀላቀሉ ይጠበቃል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...