መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና የሀድያ ሆሳዕና የፋይናንስ ሃላፊ በዋስ ተለቀቁ
ሀዲያ ሆሳዕናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

የሀድያ ሆሳዕና የፋይናንስ ሃላፊ በዋስ ተለቀቁ

አጋራ
አጋራ

ሀድያ ሆሳዕና በሶስት ቀን ውስጥ
የ15ቱን ተጨዋቾች ደመወዝ እከፍላለሁ አለ

ከደረቅ ቼክ ተያይዞ በህግ ቁጥጥር ስር የዋሉት የሀድያ ሆሳዕና የፋይናንስ ሃላፊ አቶ ተስፋዬ በዋስ ተለቀቁ።
ላለፉት 21 ቀናት በፖሊስ ቁጥጥር ስር የነበሩት አቶ ዛሬ የዋስ መብታቸው ተከብሮ ተለቀዋል።

በሌላ በኩል ሀድያ ሆሳዕና ከተከሰሰበት ክስ ነፃ ለመውጣት ከተጨዋቾቹና ጠበቃቸው አቶ ብርሃኑ በጋሻው ጋር ውይይት ማድረጋቸው ታውቋል።

ዛሬ በኢትዮዽያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ፕሬዝዳንቱ አቶ ኢሳያስ ጅራና የሀድያ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ማቲዮስ በተገኙበት በተካሄደው ድርድር ክለቡ በሶስት ቀን ውስጥ ደመወዛቸውን ለመክፈልና ቼኩን በተመለከተም በየግል ተወያይቶ ስምምነት ላይ ለመድረስ መስማማታቸው ታውቋል።

ክለቡ “ክፍያውን የምንፈጽመው ግን በፔሮል ስለሆነ ሆሳዕና መጥተው ያለባቸውን ትጥቅ መልሰው ነው” ቢልም በተጨዋቾቹና ጠበቃቸው ተቃውሞ ገጥሞታል። “እዚያ ድረስ ለመጓዝ አንተማመንም ምን እንደሚገጥመንም አናውቅም” በማለት ሌላ ጊዜ በባንክ ሲከፈለን ቆይቶ ዛሬስ ለምን በፔሮል ይሆናል? በማለት እንደማይቀበሉት ገልጸዋል።

ሀድያ ሆሳዕና አዲስ አሰልጣኝ በማድረግ ሙሉጌታ ምህረትን ቀጥሮ ዝውውር ቢያደርግም እስካሁን አለመጽደቁ ታውቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...