ሁለት የቀድሞው እግር ኳስ ተጫዋቾች በአለም አቀፉ የፊፋ የተጫዋቾች ምክክር መድረክ ላይ ለመሳተፍ ወደ ራቫት አምርዋል።
የአለም አቀፉ የእግር ኳስ የበላይ አካል ፊፋ በአፍሪካ አስተናጋጅነት በሞሮኮ ራባት ለሦስት ቀናት ያክል ለሚደረገው የፊፋ ፕሮፌሽናል ተጫዋቾች የምክክር መድረክ ላይ ሁለት ኢትዮጵያዊያን እንዲካፈሉ ጥሪ አድርጓል። ከነገ ጥቅምት 28 እስከ ጥቅምት 30 ከተለያዩ ሀገራት የተወጣጡ የተጫዋቾች ማህበራት በሚሳተፉበት በዚህ የምክክር ጉባኤ የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ እንዲሁም ለረጅም ጊዜያት የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ፀሀፊ በአሁኑ ሰአት ደግሞ ፕሬዝዳንት ሆኖ እያገለገለ የሚገኘው ኤፍሬም ወንድወሰን እና የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አማካይ እና የሴት ተጫዋቾች ማህበር እና የኢትዮ ኤሌክትሪክ የሴት ክለብ ረዳት አሰልጣኟ ቱቱ በላይ በጉባኤው ላይ ለመካፈል ወደ ስፍራው ሀገራችን ወክለው ማምራታቸው ታውቋል።



