መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ፋሲል ከነማ የተጫዋቾቹን ዉል አራዝሟል!!
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየዝውውር ዜናዎችፋሲል ከነማ

ፋሲል ከነማ የተጫዋቾቹን ዉል አራዝሟል!!

አጋራ
አጋራ

ፋሲል ከነማ በ2014 የዉድድር አመት ተጠናክሮ ለመቅረብ የነባር ተጫዋቾችን ዉል በማደስ እና አዳዲስ ተጫዋቾችን በማስፈረም ላይ ይገኛል።

እስካሁን ሦስት አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ቡድናቸዉ የቀላቀሉት ፋሲል ከነማዎች በዛሬው ዕለት የተከላካዩ ዳንኤል ዘመዴን እና የተከላካይ አማካኙን የኪሩቤል ኃይሉን ውል ለተጨማሪ አመት አራዝመዋል፡፡

ከፋሲል ከነማ ታዳጊ ቡድን የተገኘዉ ወጣቱ ተከላካይ ዳንኤል ዘመዴ ምንም እንኳን በቋሚ አሰላለፍ ዉስጥ ገብቶ መጫወት ባይችልም ከክለቡ ጋር ለቀጣይ አመታት ለመቆየት ተስማምቷል።

በተጨማሪም የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ፍሬ የሆነው የተከላካይ አማካይ ሥፍራ ተጫዋቹ ኪሩቤል ሀይሉ እንደ ዳንኤል ሁሉ ዘንድሮ በክለቡ ብዙም የመሰለፍ ዕድል እያገኘ ባይሆንም ከሻምፒዮኖቹ ጋር ለተጨማሪ አመት የሚያቆየውን ዉል ፈርሟል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...