የአጥቂ ስፍራ እጥረት የሚታይባቸው አፄዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተቃርበዋል።
ከአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ የብሔራዊ ቡድን ጉዞ በኋላ በአሁኑ ሰዓት በረዳት አሰልጣኙ አምሳሉ እስመለአለም እየተመራ የሚገኘው ፋሲል ከነማ በአጋማሹ የዝውውር መስኮት የመጀመሪያ ተጫዋቹን ለሁለተኛ የውድድር ዘመን ሊያስፈርም ከጫፍ ስለ መድረሱ ያገኘውት ጥልቅ መረጃ አመላክቷል።
ከአርባምንጭ ከተማ የተገኘው እና ከነገሌ አርሲ የከፍተኛ ሊግ በኋላ ባለፈው በ2016 የውድድር ዘመን አጋማሽ ቅዱስ ጊዮርጊስን በመቀላቀል በክለቡ ቆይታን በማድረግ ከኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጋር መተዋወቅ የቻለው አጥቂው ታምራት እያሱ ያለፉትን አንድ አመት ያደገበትን ክለብ አርባምንጭ ከተማን ሲያገልግል ቆይቷል።
በዚህ የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዘመን አርባምንጭ ከተማ በውጤት ቀውስ ውስጥ ሆኖ እየተጓዘ በደረጃ ሰንጠረዡ ግሮጌ ላይ መቀመጥ ቢችልም በሊጉ ሰባት ጎሎችን በማስቆጠር የከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ዝርዝር ውስጥ ከአቤል ያለው እና አዲስ ግደይ በአንድ ጎል አንሶ የተቀመጠው አጥቂው አርባምንጭ ከተማዎች ውሉን ለማደስ ብርቱ ጥረት ቢያደርጉም ተጫዋቹ ግን አፄዎቹን ለመቀላቀል ከጫፍ መድረሱን በጥልቀት ያደረኩት መረጃ አመላክቷል።


