የመሐል ተከላካዩ ከመቻል ጋር ተለያየ።
በአሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት የሚመራው መቻል ከአንደኛው ዙር የሊግ ውድድር በሁለተኛው ተጠናክሮ እንደሚጠነክር የሚጠበቅ ሲሆን አሁን ባገኘሁት መረጃ ከመሐል ተከላካዩ ነስረዲን ሐይሉ ጋር መለያየቱን ያገኘሁት መረጃ አመላክቷል።
የቀድሞው የገላን ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና የመሐል ተከላካይ ያለፉትን ሦስት የውድድር ዘመን ከመቻል ጋር ቆይታ ያደረገ ሲሆን አሁን መለያየቱን አረጋግጫለሁ።
ከክለቡ ጋር በተያየዘ ከሰሞኑ ከወጣት ተጫዋቾች ጋር እንደሚለያይ የሚጠበቅ ሲሆን የቀድሞው የአዳማ እና ሀዋሳ የመስመር አጥቂ ዮሴፍ ታረቀኝ ክለቡ እንዲለቀው ጥያቄ ስለማቅረቡ መረጃዎችን አግኝቻለሁ።
- ማሰታውቂያ -



