ደካማ የ19 ሳምንት ጉዞን ያደረገው ወልዋሎ አራት ተጫዋቾችን ሊለቅ ነው።
በአሰልጣኝ ግርማ ታደሠ (መንቾ) የሚመሩት እና በክረምቱ ከፍተኛ የዝውውር ወጪን ያወጡት ወልዋሎዎች በሁለተኛው ዙር ካሉበት ወራጅ ቀጠና ለመውጣት አዳዲስ ተጫዋቾች የማስፈረም ዕቅድ እንዳላቸው የሰማሁ ሲሆን አራት ተጫዋቾች ግን ክለቡን እንዲለቁ አመራሩ በግልፅ ማሳወቁን ሰምቻለሁ።
የቀድሞው ደቡብ ፓሊስ ፣ ንግድ ባንክ እና ኤሌክትሪክ የመሐል ተከላካይ ጌቱ ባፋ ፣ ከሻሸመኔ ፣ ወልዋሎን የተቀላቀለው ተከላካዩ ወጋየሁ ቡርቃ ፣ የቀድሞው የደደቢት እና ሀድያ ሆሳዕና ግብ ጠባቂ ስንታየሁ ሳልልች (ሲንባ) እና በወላይታ ድቻ እና አርባምንጭ ከተማ የምናውቀው አጥቂው ፍቃዱ መኮንን ስለመሆናቸው ያገኘሁት መረጃ ይጠቁማል።



