ከተጫዋቾቹ ጋር ሰጣገባ ውስጥ የገቡት አሰልጣኝ በቦርድ ውሳኔ መለያየት ችለዋል።
በላይሰንስ ውስንነት የተነሳ ከከፍተኛ ሊጉ ያሳደገውን አሰልጣኝ በሽር አቦደላን ተክተው በፕሪምየር ሊጉ ያለፉትን አስራ ዘጠኝ የሊግ ጨዋታዎች ሸገር ከተማን በፕሪምየር ሊጉ የመሩት አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ በተደጋጋሚ ከተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ በኋላ በመጨረሻም ከቡድኑ ተጫዋቾች ጋር በሚገቡት ሰጣ ገባ የተነሳ በመጨረሻም ከክለቡ አሰልጣኝነት ተለያይተዋል።
የዛሬ አርባ አመት በኢትዮጵያ እግር ኳስ አሰልጣኝነት ብቅ ያሉት እና በቀድሞው አጠራሩ ባንኮች የአሁኑ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ መቻል ፣ ሲዳማ ቡና ፣ አዳማ ከተማ ፣ ወላይታ ድቻ ፣ ሀድያ ሆሳዕና እና ወልዋሎን እንዲሁም የኢትዮጵያ የሴት እና የወንድ ብሔራዊ ቡድንን ያሰለጠኑት አሰልጣኙ ሸገርን ይዘው ዘጠኝ አቻ አራት ድል እና ስድስት ሽንፈትን በማስመዝገብ በደረጃ ሰንጠረዡ በ21 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ካስቀመጡት በኋላ የክለቡ ቦርድ አሰልጣኙን አሰናብቻለሁ ብሏል።


