በአሰልጣኝ ውበቱ አባቱ የሚመራው ፋሲል ከነማ በግብ ጠባቂ እና አጥቂ ቦታ ላይ ቡድኑን የሚያጠናክሩ ተጫዋቾችን የግሉ አድርጓል።
የውድድር ዘመኑን አጋማሽ በስሁል ሽረ ያሳለፈው እና በተለይም በባህርዳር ከተማ ጥሩ ጊዜን ያሳለፈው ግብ ጠባቂው ፋሲል ገብረሚካኤል አፄዎቹን ተቀላቅሏል።
በውድድር ዘመኑ በስሁል ሽረ በአራት ጨዋታዎች ብቻ የተሰለፈው ፋሲል በክለቡ ለአንድ አመት ተኩል ለመቆየት ፊርማውን አኑሯል።
ሌላኛው ፋሲል ከነማን የተቀላቀለው ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የሊጉ ሻምፒዮን የሆነው የፊት አጥቂው ቢንያም ጌታቸው ነው።
- ማሰታውቂያ -
ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በፊት በአዲስ አበባ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ያሳለፈው ቢንያም እስከ 2018 የውድድር ዘመን መጨረሻ ድረስ በክለቡ ለመቆየት ውል ፈርሟል።
ፋሲል ከነማ የሁለተኛ ዙር ቀዳሚ ጨዋታውን ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ያደርጋል።


