የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር መርሀግብር ዛሬ በአዳማ እና በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሜዳዎች ላይ እየተደረጉ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሜዳ ላይ ፋሲል ከነማ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 2ለ0 እየተመራ የሚገኝ ሲሆን የፋሲሉ ጊዜያዊ አሰልጣኝ አምሳሉ እስመለአለም አፄዎቹን እየመሩ አይገኙም። ይህንን ጉዳይ ለማጣራት ሞክሬ ባገኘሁት መረጃ መሠረት አሰልጣኝ አምሳሉ እስመለአም ከመስመር አጥቂው ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ እና ሀብታሙ ተከስተ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ቡድኑ ከሳምንታት በፊት ወደ ልምምድ ሲመለስ አለማሰራታቸውን እና በዛሬውም ጨዋታ በሜዳ ላይ ተገኝተው ቡድናቸው እየመሩ እንደማይገኝ አረጋግጫለሁ።
በረዳቱ ኤልመዲን አህመድ እየተመራ የሚገኘው ቡድኑ በአሁኑ ሰዓት በንግድ ባንክ እየተመራ ይገኛል።
በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ዝርዝር ሀሳቦች ካሉ እመለሳለሁ !


