ሊግ ካምፓኒው
29 ሚሊየን ብር ገቢ እጠብቃለሁ አለ
* የተጨዋቾች የደመወዝ ገደብ
ከ2014 ጀምሮ እንዲነሳ ተወስኗል…
በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ስብሰባውን እያደረገ ያለው የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ ካምፓኒ በ2013 ከሊጉ ስያሜ 8 ሚሊየን ብር እንደሚጠብቅ ገልጿል፡፡
ካምፓኒው ከክለቦች ክፍያ ከቲቪ መብትና ከሊጉ ስያሜ ጋር በአጠቃላይ 29 ሚሊየን ብር እንደሚጠብቅም አመራሮቹ ገልጸዋል፡፡ካምፓኒው ከዚህ በኋላም 5 ሰራተኛ እንደሚቀጥርና የራሱን ቢሮ እንደሚከራይ የተነገረ ሲሆን ሲያወዛግብ የነበረው የተጨዋቾች የ50 ሺ ብር የደመወዝ ገደብ በ2013 ባለበት እንዲቀጥል ከ2014 ጀምሮ ሁሉም እንደአቅሙ እንዲከፍል ተወስኗል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በስያሜያቸው ጥያቄ የተነሳባቸው ክለቦች በራሳቸው ፍቃድ ስያሜያቸውን እንዲቀይሩ መወሰኑን በዝግ የተካሄደውን ስብሰባ ከፍተን ማረጋገጥ ችለናል፡፡
አስተያየት ይስጡ