የወጣት ተጫዋቾቻቸውን ውል ለበርካታ ዓመታት በማራዘም ላይ የሚገኙት ኢትዮጵያ ቡናዎች አሁን ደግሞ የወሳኙን ተከላካያቸውን ወንድሜነህ ደረጄ ውል ለአራት ዓመታት ማራዘማቸውን የተጫዋቹ ወኪል ገልጿል ።
ባሳለፍነው ዓመት በኢትዮጵያ ቡና ምርጥ አቋም ካሳዩ ተጫዋቾች አንዱ ወንድሜነህ ደረጄ ሲሆን ክለቡም ይህን በማየት ከአቡበከር ነስሩ፣ አማኑኤል ዮሃንስ እና ሚኪያስ መኮንን ቀጥሎ በኢትዮጵያ ቡና ቤት ለረጅም ጊዜ የሚያቆየው ውል አቅርቦለታል ።
- ማሰታውቂያ -
ከጣና ሞገዶቹ ኢትዮጵያ ቡናን የተቀላቀለው ወጣቱ ተከላካይ ወንድሜነህ ደረጄ እስከ 2017 የውድድር ዓመት በቡናማዎቹ ቤት የሚቆይ ይሆናል ።