መነሻ ገጽ ዜናዎች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ዛሬ መስከረም 11 ቀን 2013ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ባካሄዱት ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፈዋል፡፡

1ኛ ካፍ በ Zone በሚያካሂዳቸው የማጣሪያ ውድድሮች ላይ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች እና ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች በሴካፋ ዞን በሚካሄዱት ውድድሮች በቀጣይ ሴካፋ በሚያወጣው መርሃ ግብር መሰረት እንዲሳተፉ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ CECAFA ውድድር በዚህ ዓመት እንዲሳተፍ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ወስኗል፡፡

2ኛ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ ባደረገው ስብሰባ የ Club Licensing ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ቴዎድሮስ ፍራንኮ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቴክኒክ ዳይሬክተር ሆነው እንዲሰሩ የተወሰነ ሲሆን የሥራ አፈፃፀማቸው እየተገመገመ በየጊዜው ለስራ አስፈፃሚ እንዲቀርብ ተወስኗል፡፡
3ኛ የቀድሞ የብሔራዊ ቡድን እና የኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ክለብ ግብ ጠባቂ የነበረው ይልማ ከበደ (ጃሬ) በደረሰበት ህመም በአሁን ሰዓት ፓራላይዝድ ሆኖ ስለሚገኝ ለሕክምና እንዲረዳው የብር 50,000.00/ሀምሳ ሺህ ብር/ ድጋፍ እንዲደረግለት ተወስኗል፡፡

4ኛ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኞችን በተመለከተ የቴክኒክ ኮሚቴው አሉኝ የሚላቸውን ምክረ-ሀሳቦችን በማዘጋጀት ለሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው እንዲያቀርብ በመወሰን የዛሬው ስብሰባ ተጠናቋል።

via- EFF OFFICIAL

 

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...