👉“ቅጣቱ ከውላችን ውጪ በመሆኑ አልቀበለውም”
አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ
👉ዛሬ ምሽት ወደ አሜሪካ ይሄዳል
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሀዋሳ የዘጠኝ ሳምንት ቆይታ በ16 ነጥብ 6ኛ ደረጃ የያዘው ኢትዮጵያ ቡና የስራ አመራር ቦርድ የአሰልጣኝ ካሳዬ አራጌን የአምስት ቀን ደመወዝ ቀጣ።
ከታማኝ ምንጭ በተገኘ መረጃ በአምስተኛው ሳምንት ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና በወላይታ ድቻ 3ለ1 መሸነፉን ተከትሎ የክለቡ አመራር ለአሰልጣኝ ካሳዬ ውጤቱን እንዲያስተካክል የሚያሳስብ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ቢያዘጋጅም አሰልጣኙ ደብዳቤውን ለመቀበል ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። ነገር ግን በተከታታይ የነበረውን የጅማ አባጅፋር፣ የመከላከያ፣ የድሬዳዋ ከተማና የወልቂጤ ከተማ ጨዋታዎችን ማሸነፉን ተከትሎ ጉዳዩ ሳይነሳ ቆይቷል። ነገር በ9ኛ ሳምንት በሀድያ ሆሳዕና መሸነፉን ተከትሎ “የተዘጋጀውን ደብዳቤ አለመቀበል የዲሲፕሊን ጥሰት ነው” በሚል ቦርዱ የአምስት ቀን ደመወዙን እንዲቀጣ ወስኖበታል። አሰልጣኝ ካሳዬ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤውን ከሳምንታት ቆይታ በኋላ ትናንት ምሽት መቀበሉ ታውቋል።
አሰልጣኙ የሊጉን መቋረጥ ተከትሎ ዛሬ ምሽት ለዕረፍት ወደ አሜሪካ የሚጓዝ መሆኑ ታውቋል።
አስተያየት ይስጡ