የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር የፋይናንስ አጣሪ ተቆጣጣሪ ኮሚቴ በ2017 ዝውውር የፈጸሙ ተጨዋቾችን በሙሉ የዝውውር ውልን ኦንደሚመረምር ይፋ ሆነ።
ዛሬ ቀትር ላይ ከቤስት ዌስተርን ፕሪሚየም ሆቴል የሊጉ የቦርድ ፕሬዝዳንት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞና ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ ክፍሌ ሰይፈ በጋራ በሰጡት መግለጫ መገናኛ ብዙሃኑ ለሰጡት ትኩረትና ላደረጉት ድጋፍ አመስግነዋል።
እንደ አመራሮቹ መግለጫ በምርመራ ሂደቱ ክህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋብዘን አይተው ተረድተው ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸውናል በሂደቱም ለኢትዮጵያዊ ችግር ኢትዮጵያዊ የሆነ የፋይናንስ አስተዳደር መሰረት እንዲይዝ ተደጋጋሚ ጊዜ ተወያይተን የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላትን አነጋግረናል ሲሉ ሂደቱን አስረድተዋል።
ከፍተኛ ደመወዝ የሚከፈላቸው ተጨዋቾች 300ሺህ ብር ሆኖ የባንክ አካውንታቸው ሲታይ እስከ 7 ሚሊዮን ብር ልዩነት አምጥቷል። በልዩነቱ ከፍተኛ
6.7 ሚሊዮን ብር ዝቅተኛ 1.4 ሚሊዮን ብር ልዩነት ማሳየቱን በመግለጽ ውሳኔው ትክክል ነው ያልሰራነው የምንጸጸትበት ምክንያት የለም ሲሉ አመራሮቹ ገልጸዋል። እንደ አመራሮቹ ገለጻ ውሳኔ ከተሰጠባቸው አራት ክለቦች ውጪ በሌሎች ሁለት ክለቦችና 10 ተጨዋቾች ላይም ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።
- ማሰታውቂያ -
ይህን ከባድ የምርመራ ስራ የሚሰራው ኢነሳ በርካታ ሀገራዊ አጀንዳዎች ስላሉበት የመዘግየት ሂደት መከሰቱን የተናገሩት አመራሮቹ ለወጣው ደንብና መመሪያ ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ሙሉ ድጋፍ አለን ሲሉ ተናግረዋል።
ፕሪሚየር ሊጉ አዲስበባ ላይ እንዲካሄድ ለማድረግ የ ሲካሄድ የነበረው ምክክር ተቋርጧል እንደገና ለመጀመር ብንፈልግም የሚመለከተው አካል ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል ሲሉ አመራሮቹ ገልጸዋል።
አመራሮቹ የትግራይ ክለቦች የሆኑት ሁለት ክለቦች ከጦርነቱ በፊት የሚደርሳቸውን ገንዘብ መውሰዳቸውን በመግለጽ ሊጉ ጋር ምንም ቀሪ ገንዘብ እንደሌላቸው ገልጸዋል። ያም ሆኖ መቀለ 70 እንደርታ ዠገቢና የሚካፈሉት ገንዘብ ባይኖራቸውም የፌዴሬሽኑ አባል በመሆናቸው አባል የሚቀጣውን ተቀጥተዋል ሲሉ አብራርተዋል።
ከዲ ኤስ ቲቪ ጋር ውላለው ውል የተጠየቁት አመረሮች ዲ ኤስ ቲቪ በሀገሩ በደረሰበት ኪሳራ ዘንድሮ የሚጠበቅበትን ከፍሎ ለመለያየት ተስማምተናል በቀጣይ አመታት ግን የሚተላለፍበትን ጣቢያ ለመለየት 3 የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን አነጋግረን እየሰራን ነው ከሌሎች ካምፓኒዎች ጋር ለመደራደር ዲሎይት የተባለ ተቋም ሊጉን እንዲያጠና እያረግን ነው ሲሉ አብራርተዋል።


