*…. አሁንም ኮሚሽነሯ ፍቅረገነት አስማማው ናት…. በሪፖርቷ አርቢትሩን በድጋሚ ታድነው ይሆን ..?
*…. የሊግ ኩባንያውና የዳኞች ኮሚቴ አለመከባበር ቀጥሏል….
ኢትዮ ኤሌክትሪክ 3 ነጥብ የማገኝበት ንጹህ ግብ ተሽሮብኛል ሲል ለሊግ ኩባንያ ከሰሰ።
ትላንት የተካሄደው የ ኢትዮ ኤሌክትሪክና ስሁል ሽረ ጨዋታ 0ለ0 የተጠናቀቀ ሲሆን ኢትዮ ኤሌክትሪክ 53ኛ ደቂቃም ላይ ያስቆጠረውና ከንከኪ የጸዳ ግብ በአርቢትሩ መሻሩ ኢትዮ ኤሌክትሪኮችን አበሳጭቷል።
- ማሰታውቂያ -
ኢትዮ ኤሌክትሪኮች ከጨዋታው በኋላ ህጉን ተከትለው ክስ ያስያዙ ሲሆን የጨዋታው ኮሚሽነር ፍቅረገነት አስማማው ሪፖርት ይጠበቃል። አርቢትሩ ሲከሰስ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊሶች ከሲዳማ ቡና ጋር በነበረ ጨዋታ ፍጹም ቅጣት ምት ከለከለን በማለት ቢከሱም ኮሚሽነሯ በሪፖርቷ ነጠቡን ከ7 በላይ አድርጋ በመስጠት ዳኛውን ከቅጣት እንዳስመለጠችው የሚወጡ መረጃዎች ይገልጻሉ።
በዚህም ጨዋታ ኮሚሽነሯ ፍቅረገነት የዛሬ አመት ፌዴረል አርቢትር ባህሩ ተካ ላይ የጠችውን ትክክለኛ ሪፖርት በኢንተርናሽናል አርቢትር ኤፍሬም ደበሌ ላይ ማሳየት አለመቻሏ በጫና ነገም እንድትመደብ በማሰብ ይሆን ..? የሚል ቅሬታ አስነስቷል።
ፈረሰኞቹ እስካሁን በክሳቸው ላይ ምላሽ ያላገኙ ሲሆን ሊግ ኩባንያው የዳኛ ኮሚቴን በፍጥነት ምላሽ እንዲሰጥ የማስገደድ አቅሙ መዳከሙን ወይም አለመከባበራቸውን የሚያሳይ ነው በሚል የስፖርት ቤተሰቡ መነጋገሪያ ሆኗ። ሌላ አርቢትር ቢሆን ኮሚቴው ዝም ይል ይሆን ..? ተበደልን የሚሉ ክለቦች ሳይኖሩ ተበድላችኋል በማለት ዳኞችን ሲያባርር አልታየም ወይ በሚል ዳኛ ኮሚቴ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖችም አሉ።
የአክሲዮን ማህበሩ የውድድርና ስነስርጻት ኮሚቴ የተሳሳተ ሪፖርት ባቀረቡ ኮሚሽነሮች ላይ ዝምታ መምረጡ የቀረበ ቅሬታ ዙሪያ የዳኛ ኮሚቴን ቶሎ እንድትመልሱ ብሎ አለማስገደዱ በፍትህ መዛባት ጥያቄ እንዳይነሳበት ያሸጋል።
ለጉዳዩ ቅርበት ያለው ምንጭ እንደገለጸው ዳኞች ስለተሳሳቱ ይታገዱ ይባረሩ የሚል አቋም ባይኖርም ሁሉም ዳኞች እኩል እንዲታዩ ለቀረበ ቅሬታ ዙሪያ ከማድበስበስ ቶሎ ምላሽ መስጠት ለፍትህ መከበር ያለውን አቋም ያሳያልና ዳኞች ኮሚቴ ፈጣን ምላሽ መስጠት ይጠበቅበታል በማለት አስተያየት ሰጥቷል።


