የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አብዛኞቹ ክለቦች አሁንም ደመወዝ እየከፈሉ አለመሆኑ የክለቦቹ ወርሃዊ ሪፖርት አመለከተ።
የሊግ ኩባንያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ እንደተናገሩት እየቀረበልን ካለው የክለቦቹ ሪፖርት አሁንም አብዛኞቹ ክለቦች ደመወዝ እየከፈሉ አይደለም ሲሉ ተናግረዋል።
አት ክፍሌ ሲያብራሩ ከክለቦቹ የሚጠበቀው ወርሃዊ ሪፖርት ነው ከፍለውም ከሆነ ከፍለናል ካልከፈሉም አልከፈልንም ብለው ሪፖርት ማድረግ የግድ አለባቸው ያንን እያደረጉ ባሉት ክለቦች እንዳየነው አብዛኞቹ ደመወዝ አልከፈሉም ይሄ ለሊጉ ስጋት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
እንደ አቶ ክፍሌ ትዝብት በኛ ሀገር እግርኳስ ዋንጫ በወሰደና በወረደው ክለብ መሃል ያለው ልዩነት ገንዘቡ እንጂ እንደ ሀገር ለውጥ የለውም ውጤት በሌለው እግርኳስ ላይ ብዙ ማውራት ያሳፍራል” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
- ማሰታውቂያ -
እየቀረበላቸው ስላለው ጥቆማ የተነገሩት አቶ ክፍሌ
” ወጣት ነን እኛን አይፈልጉም የሚያቋቸውን ብቻ ነው የሚጠቀሙት ኳስ እንችላለን አቅም አለን ለፍተናል ቦታ ግን አጣን ለምን ይሄ አይስተካከልም የሚል ቅሬታ እየመጣልን ነው ወጣቶቹ ቦታ ያጡት ባለው በጥቅም ትስስር ነው ይሄ ደግሞ በገንዘብ በክፍያ የመጣ በመሆኑ መበጠስ አለበት ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ክፍሌ የምስረታ ዘመናቸውን ስናይ በ1940
በ1950 የሆኑ ክለቦች አሉ ያኔ ተመስርተው ተቋማዊ መልክ የሌላቸው ብዙ ክለቦች አይተናል አሁን ድረስ ዘመናዊነት ያልተላበሱ መሆናቸው ያሳዝናል በዚህ ዘመነ
የክለብ ላይሰንሲንግ መጠየቁ ያሳፍራል ሲሉ ተናግረዋል።
ከዲ ኤስ ቲቪ ጋር በተያያዘ እንደገለጹት
ከዲ.ኤስ. ቲቪ ጋር የነበረን ውል ዘንድሮ ይጠናቀቃል ከተስማማን ውል እናድሳለን ካልሆነ ጨረታ እናወጣለን ያም ሆኖ በ2018 ውድድሩ የቴሌቪዥን ስርጭት ያጣል ብለን አንሰጋም ስጋታችን ዲ ኤስ ቲቪ የሚከፈለንን ገንዘብ ያህል ላናገኝ እንችላለን የሚለው ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።


