አሰልጣኝ ኤርሚያስ በቀለ /ሮማሪዮ/
መብቴን ጥሷል ያለውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንን በመደበኛ ፍርድ ቤት ከሰሰ።
በሴቶች እግርኳስ ላይ ከማይረሱት አሰልጣኞች አንዱ የሆነው ኤርሚያስ በቀለ /ሮማሪዮ/ የካፍ ኤ ላይሰንስ ለማግኘት ኮርስ እየወሰዱ ያሉ 25 አሰልጣኞች ምርጫ ውጪ በመደረግ ተበድያለሁ መብቴ ተጥሷል ሲል የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ባህሩ ጥላሁንና የፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ልማት ባለሙያ አቶ ደረሰ እሸቱ ላይ ልደታ ፍርድ ቤት ክስ መመስረቱ ታውቋል።
ሮማሪዮ ለፌዴሬል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ያቀረበው ክስ የፊታችን ሰኞ የካቲት 16/2018 ከቀኑ 8 ሰዓት መታየት እንደሚጀምር ታውቋል።


