የቀኝ መስመር ተከላካዩ ወልዋሎን በይፋ ተቀላቅሏል።
በደመወዝ ክፍያ ስማቸው በተደጋጋሚ እየተነሳ የሚገኙት እና በተደጋጋሚ ስማቸው በጉዳዩ ላይ እየተነሳ የሚገኘው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲዎች በአጋማሹ የመጀመሪያ ተጫዋቻቸውን የግላቸው አድርገዋል። የቀድሞው የሰበታ ከተማ ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ፣ ወልቂጤ ከተማ ጋር በፕሪምየር ሊጉ መጫወት የቻለው የቀኝ መስመር ተከላካዩ ጌቱ ሀይለማርያም ከከፍተኛ ሊጉ ሻሸመኔ ከተማ በኋላ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ከአንድ አመት ከግማሽ ወራቶች በኋላ በመመለስ ወልዋሎን መቀላቀል ችሏል።
የሁለተኛው ዙር የሊጉ መርሀግብር የፊታችን ቅዳሜ ሲጀመር ወልዋሎ የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን የሚገጥም ይሆናል።



