ኢንተርናሽናል አርቢትር ባህሩ ተካን በማሰናበት ኢንተርናሽናል አርቢትር ቴዎድሮስ ምትኩን ባላየ ማለፉ አነጋጋሪ ሆኗል።
ብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴ ውጤት ለውጧል ያለውን ኢንተርናሽናል አርቢቴር ባህሩ ተካን አሰናብቻለሁ ብሏል። ከታማኝ ምንጮች ሀትሪክ ባገኘችው መረጃ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከምድረ ገነት ሽረ ጋር 0ለ0 በተለያዩበት ጨዋታ ፈረሰኞቹ ፍጹም ጥላሁን በጭማሪ ደቂቃ ላይ ያስቆጠረውን ንጹህ ጎል መሻሩን ይታወሳል በዚህም የተነሳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅሬታን በማሰናበት ደብዳቤ ማስገባታቸው ይታወሳል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን የዳኞች ኮሚቴ ትላንት ፌዴራል አርቢትር አባይነህ ሙላትን በማስቀረት ኢንተርናሽናል ዳኛ ባህሩ ተካን ከምደባው ውጪ ማድረጉ ታውቋል።
አርባምንጭ ከተማ ከፋሲል ከነማ ጋር ሲጫወቱ የፋሲል ከነማው አጥሺ ቃልኪዳን ዘላለም በእጁ ያስቆጠረውን ጎል ያጸደቀውና ውጤት ለዋጭ ስህተት የሰራው ኢንተርናሽናል ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩን ግን ባላየ አልፎታል። ተጫዋቹ በእጁ ማስቆጠሩን አምኖ በጨዋነት ይቅርታ በጠየቀበት ፍጥጥ ያለ እውነት ዳኞችን ይለያል በዕኩል ዐይን አያይም የሚባለው ኮሚቴም በዝምታ አልፎታል። ዳኛ ሆኖ ዕኩልነትን የማይተገበር ኮሚቴ ነው በሚልም የሚተቸው ብሄራዊ ዳኞች ኮሚቴም ሆነ የፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት ዝም ማለታቸው ቅሬታ ፈጥሯል።


