አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ሁለት ረዳቶቹን ከሀገራችን ወስዷል።
የደቡብ ሱዳኑን ክለብ ጃሙስን በመረከብ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በድል የጀመሩት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ሁለት ባለሙያዎችን ከሀገራችን በረዳት አሰልጣኝነት እና በቪዲዮ ተንታኝነት ወስደዋቸዋል። የቀድሞው የወልቂጤ ከተማ ፣ ባህርዳር ከተማ እና ጂማ አባቡና አሰልጣኝ እና በአሁኑ ሰዓት በእንግሊዝ ማንችስተር ከተማ ውስጥ ወጣቶችን እያሰለጠኑ የሚገኙት የአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ወንድም የሆኑት አሰልጣኝ ፋንታዬ አባተ እና የባህርዳር ከተማ የቪዲዮ አናሊሲስት ካለፈው አመት ጀምሮ ደግሞ የአሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛው ረዳት ሆኖ ላለፉት ስድስት አመታት በክለቡ እየሰሩ የነበሩት መብራቱ ሀብቱ የአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ረዳት እና የቪዲዮ አናሊሲስ ባለሙያ ሆኖ እንዲሰራ አሰልጣኙ ወደ ጁባ ሁለቱንም ወስደዋቸዋል።
አሰልጣኝ ፋንታዬ የአውሮፓ ዩኤፋ ቢ ላይሰንስ ሲኖራቸው አሰልጣኝ እና አናሊሲስቱ መብራቱ በበኩላቸው የዩኤፋ ኤ ላይሰንስ እና የካፍ ቢ ላይሰንስ ባለቤቶች ናቸው።


