ዋሊያዎቹ ቤንጋዚ ሊቢያ ላይ ከሱዳን ጋር ባለባቸው ጨዋታ የመጀመሪያ ግጥሚያውን በዝግ እንዲካሄድ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተነገረ።
ዋሊያዎቹ ከሱዳን ጋር ላለባቸው ጨዋታ ወደ ሊቢያ ቤንጋዚ ከማቅናታቸው በፊት ዛሬ በፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት በተሰጠ መግለጫ ላይ ቡድኑ ቤንጋዚ ላይ ባለሜዳ በሚሆንበት ጨዋታ ላይ ሀገሪቱ ሊቢያ በመሆኗኗ በርካታ ሱዳናዊያን በመኖራቸው የሜዳ አድቫንቴጅ እንዳይወሰድ ሲባል ጨዋታው በዝግ እንዲሆን ለካፍ ጠይቀናል ሲሉ ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን ገልጸዋል።
ቡድኑ ከታህሳስ 3/2017 ጀምሮ ጠንካራ ዝግጅት እያደረገ መቆየቱን የገልጹት የዋሊያዎቹ አሰልጣኝ የወዳጅነት ጨዋታ ባለመኖሩ. ከ20 አመት በታች ቡድን ጋር ተጫውቶ 4ለ1 ያሸነፈ መሆኑና ከአጨዋወት አንንጻር ጥሩ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው እንደተናገሩት የቻን ውድድር ይቀጥል ይቁም የሚል ውይይት ኬንያ ላይ ተደርጎ እንዲቀጥል በመወሰኑና፡ውሳኔው ዘግይቶ የደረሰን በመሆኑ ከዚያ በተጨማሪ የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ያልተቻለው በፊፋ ካላንዳር መሰረት የሚካሄድ ውድድር ባለመሆኑ ነው ሲሉ ገልጸዋል።


