መነሻ ገጽ ዋልያዎቹ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውላቸውን አራዘሙ
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውላቸውን አራዘሙ

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ውላቸውን ለማራዘም ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በዛሬው ዕለት ስምምነት ፈፅመዋል።

በ2013 ዓ.ም ብሔራዊ ቡድናችንን በመረከብ ያለፉትን ሁለት ዓመታት በስራ ላይ የቆዩት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በቆይታቸው ብሔራዊ ቡድናችን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ከስምንት ዓመት በኋላ የተመለሰ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ በአልጄርያ ለሚከናወነው የአፍሪካ ሀገራት ቻምፒዮንሺፕ (ቻን) ከስድስት ዓመት ቆይታ በኋላ የውድድር ተሳትፎ አሳክቷል። አሰልጣኙ ውላቸው መጠናቀቁን ተከትሎም ለቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት (እስከ መስከረም 2017) በዋና አሰልጣኝነት እንዲቀጥሉ በዛሬው ዕለት የውል ስምምነት ተፈራርመዋል።

ከውል ማራዘም ጋር የተያያዙ ዝርዝሮች እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለቻን ውድድር ማለፉን የተመለከተ ማብራርያ ሰኞ መስከረም 9/2015 በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከቀኑ 9፡00 ላይ ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...