መነሻ ገጽ አፍሪካ ዋንጫ የካሜሩን የአፍሪካ ዋንጫ የጉዞ ዋጋ ማሻሻያ ተደረገበት
አፍሪካ ዋንጫዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የካሜሩን የአፍሪካ ዋንጫ የጉዞ ዋጋ ማሻሻያ ተደረገበት

አጋራ
አጋራ

👉 ለጭማሪው የኢኮኖሚ ጫናው
ምክንያት ሆኗል…

ከዋሊያዎቹ ጋር ወደ ካሜሩን ከሚጓዙ 500 ደጋፊዎች መሃል ለመሆን በርካታ ደጋፊዎች እየተመዘገቡ መሆናቸው ታውቋል።

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ከሲሳይ አድርሴ ፕሮሞሽን ጋር በመተባበር ይህን ምዝገባ እያከናወነ ሲሆን ቁጥራቸውበርካታ የስፖርት ቤተሰብ እየተመዘገበ በመሆኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምዝገባው ሊጠናቀቅ እንደሚችል ገልጸዋል።

ከጃንዋሪ 9//2022 እስከ ፌብሩዋሪ 6/2022 በካሜሩን ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ከስምንት አመታት ቆይታ በኋላ የተመለሱትን ዋሊያዎቹን ለመደገፍና የኢትዮጵያን መልካም ስም ለመላው አለም ለማሳየት አጀንዳ ያለው ይኸው ጉዞ በስኬት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል። ለ10ቀናት ቀሚኖረው ቆይታ ሙሉ ወጪያቸው ተችሎ ከሚሄዱት 25 ጋዜጠኞች ውጪ ሌሎች የአውሮፕላን የምግብና የማረፊያ ፣ በካሜሩን ቆይታ ለሚንቀሳቀሱበት የመኪናና የስታዲየም መግቢያ ወጪን ችሎ 68 ሺህ 223 ብር እንደሚከፈል ታውቋል።

አዘጋጅ አካሉ እንደገለጸው አስቀድሞ ይፋ ተደርጎ በነበረው የ55 ሺህ 223 ብር ክፍያ ላይ ጭማሪ የተደረገው በተፈጠረው ከሰሞኑ በተፈጠረው የኢኮኖሚ ጫና ምክንያት ማሻሻያ ማድረግ በማስፈለጉ ነው።

ሲሳይ አድርሴ ፕሮሞሽንም አስቀድመው ተመዝግበው የነበሩት ደጋፊዎችን ቢሮ ድረስ በመጥራትና ሁኔታውን በማስረዳት መግባባት ላይ የደረሱ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ በአስገዳጅ ምክንያት በተሻሻለው 68ሺህ 223 ብር ምዝገባው እንደሚቀጥል ታውቋል

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...