መነሻ ገጽ ዜናዎች የድሬዳዋ ከተማ ዋና አሰልጣኝ ፍሰሃ ጥዑመልሳን በ2013 ዓ.ም የዉድድር ዘመን አብረዋቸው የሚሰሩ ምክተሎቻቸውን አሳወቁ፡፡
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግድሬዳዋ ከተማ

የድሬዳዋ ከተማ ዋና አሰልጣኝ ፍሰሃ ጥዑመልሳን በ2013 ዓ.ም የዉድድር ዘመን አብረዋቸው የሚሰሩ ምክተሎቻቸውን አሳወቁ፡፡

አጋራ
አጋራ

 

አምና የቀድሞ የክለቡ አሰልጣኝ ሲምዖን አባይ ከክለቡ መሰናበታቸውን ተከትሎ ቡድኑን በጊዜያዊነት ይዞ የነበረው ፍሰሃ ጥዑመልሳን ዘንድሮ በዋና አሰልጣኝነት ከተሸመ ቡኃላ አብረዋቸው የሚሰሩ ምክትሎቻቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡

በዚህም መሠረት የክለቡ ቴክኒክ ኮሚቴ በመሆን ሲያገለግል የነበረው ቶፊቅ ኢደሪስ ም/አሰልጣኝ ሲሆን ክለቡ በአዲስ መልክ በ1997 ዓ.ም ሲመሰረት ተጫዋች በመሆን ያሳለፈው ኤፍሬም ጌታሁን ሶስተኛ አሰልጣኝ መሆናቸውን አሳዉቀዋል፡፡

ም/አሰልጣኝ በመሆን የተመደቡት ቶፊቅ ኢድሪስ ከድሬዳዋ ከተማ ዉጭ ናሽናል ሲሚንትን በከፍተኛ ዲቪዚዮን በም/አሰልጣኝነትና በዋና አሰልጣኝነት አገልግሏል ቶፊቅ በተጨማሪም የኮተን ቡድን በድሬዳዋ ከፍተኛ ዲቪዚዮን የሶስት ዋንጫ ባለቤት እነዲሆን ያስቻለ አሰልጣኝ ነው፡፡

ሶስተኛ አሰልጣኝ በመሆን የተመደቡት ኤፍሬም ጌታሁን የድሬዳዋ ምርጥ ቡድኖችን በማሰልጠን በተለያዩ የክልል ሻምፒዮና ላይ የተሳተፈ ሲሆን ከዚህ ዉጭም የአሊሃብቴ እና ቀበሌ 06 ቡድኖችን ማሰልጠን ችሏል፡፡

ዘንድሮ ዋና አሰልጣኝ በመሆን የተሸሙት አሰልጣኝ ፍሰሃ ጥዑመልሳን ከም/አሰልጣኞቻቸው ጋር በመሆን ቡድኑን የሊጉ ተፎካካሪ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...