መነሻ ገጽ ባህርዳር ከተማ ባዬ ገዛኸኝ በመጨረሻም የባህርዳር ከነማ ንብረት መሆኑ ተረጋግጧል
ባህርዳር ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ባዬ ገዛኸኝ በመጨረሻም የባህርዳር ከነማ ንብረት መሆኑ ተረጋግጧል

አጋራ
አጋራ

 

*.. ከዋሊያዎቹ በጉዳት እረፍት የተሠጠው ባዬ
ለፊርማ እንዴት መጣ የሚለው እያነጋገረ ነው…

በኢትዮጲያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ተገኝቶ ያልፈረመ ተጨዋች ለሌላ ክለብ ቢፈርምም መጀመሪያ አስፈረምኩ በሚለው ክለብ ሊከሰስ አይችልም.. ተጨዋቹም ያስፈረመው ክለብ ሃሳቤን ለውጫለሁ ቢል ክለቡን መክሰስ አይችልም ይሄ በቅርብ አመታት የተጀመረ አካሄድ ግን በሚገርም ሁኔታ የተጨዋቾችን የቱሪስት ፊርማ እያሳየን ነው.. ፌዴሬሽን ሳይሄዱ ሁለት ክለቦች ጋር ሄደው ፈረሙ የሚለው ዜና የተለመደ ሆኗል፡፡

ከደቂቃዎች በፊት የደረሰኝ የባዬ ገዛኸኝ ፊርማ ግን በዝውውር ሃትሪክ የሰራ መሆኑን አሳይቷል፡፡ ፌዴሬሽን ሳይመጣ የወላይታ ዲቻውን ውል ማደሱን በፊርማው አረጋገጠ ከሳምንታት በኋላ ደግሞ የተሻለ አቀረበልኝ ላለው ወልቂጠ ከተማ ፈረመ፡፡

የዝውውር መስኮቱ ሲከፈት ማጽናት የሚጠበቅባቸው ወልቂጤዎች ግን ዛሬ ሌላ ተጨዋች ፊርማ ሊያስፈርሙ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ሲገኙ ፈርሞልናል ያሉት ባዬ ገዛኸኝ አካሄዱን ላወቀበት ባህርዳር ከተማ ፊርማውን አኑሮና የአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ህጋዊ ተጨዋችነት አረጋግጦ ሲወጣ ተገናኙ…እንዴት ብሎ እንዳመለጣቸው እግዜር ይወቀው ብሎኛል ምንጬ…እናም የዝውውር ፊርማውን በሀትሪክ ያጸናው ባዬ የባህርዳር ከተማ ንብረት ሆኗል፡፡

ከባዬ ዜና ሳንወጣ ህመም ገጥሞኛል በሚል በአሰልጣኝ ውበቱ አገግመህ ና ፍቃድ ያገኘው ተጨዋቹ ለፊርማው ሲባል እንዴት መጣ የሚለው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ የተጨዋቹ ስልክ ዝግ በመሆኑ ግን ምላሹን ማግኘት አልተቻለም፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...

መቐለ 70 እንደርታዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዘርአይ ሙሉ በቴክኒክ አማካሪነት ወደ ፕሪምየር ሊጉ ተመልሷል

አሰልጣኙን ያሰናበተው መቐለ 70 እንደርታ ሌላ ሹመትን ፈፅሟል። በያዝነዉ የዉድድር አመት ደካማ...